Saturday, March 16, 2013

አራት የኦሮሞ ድርጅቶች ነገ በሚኒሶታ ቀጣይ የትግል ራዕያቸውን ያሳውቃሉ


ዘ-ሐበሻ) በኦሮሞ ሕዝብ ቀጣይ የትግል ጉዞ ላይ ለመወያየት በሚል የተዘጋጀውና ሁሉንም የኦሮሞ ድርጅቶች ያሳተፈው ኮንፍረንስ ነገ ቅዳሜ ማርች 16 ቀን 2013 በሚኒሶታ እንደሚደረግ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ።
ራሱን የ’ኦሮሞ-አሜሪካውያን ሲትዝን ካውንስል” በሚል የሚጠራው ተቋም ባዘጋጀው በዚህ ትልቅ ኮንፈረንስ ላይ በጀነራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ፣ በኦቦ ሌንጮ ለታ የሚመራው የኦሮሞ ዲያሎግ ፎረም፣ በኦቦ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው ኦነግ፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ኃይል ተወካዮች እና ጃዋር መሐምድ እንደሚገኙ የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
በዚህ ስብሰባ ላይ ለመገኘትም ኦቦ ሌንጮ ለታና ጃዋር ሙሐምድ ሚኒሶታ እንደገቡ ታውቋል።
የኦሮሞ ሕብዝ ትግል ቀጣዩ ጉዞ በሚል በተዘጋጀው በዚህ ኮንፈረንስ ላይ የተጋበዙት ድርክቶች ድርጅቶች ለኦሮሞ ሕዝብ ቀጣይ የትግል አካሄድ ያላቸውን ራዕይ እንደሚያስረዱ ይጠበቃል። በጀነራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በጋራ ትክክለኛው ፌደራሊዝም የሚተገበርባትን ኢትዮጵያ ለመፍጠር እንደሚታገል ቀድሞ ያሳወቀ ሲሆን በዚህ ዙሪያ ድርጅቱን ወክለው የሚቀርቡት ኦቦ ቃሲም አባነሻ ሰፊ ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላም በኩል አዲስ የትግል ራዕይ ይዞ የመጣው የኦሮሞ ዲያሎግ ፎረም በኦቦ ሌንጮ ለታ በኩል ወደፊት ስለሚከተለው የትግል ራዕይ በተለም በተለያዩ ዓለማት እየተዟዟረ የኦሮሞ ሕዝብ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር በጋራ ታግሎ ወያኔን መጣል እንዳለበት ሲያስረዳና ሲወያይበት የነበረውን ጉዳይ ያብራራል ተብሎ ይጠበቃል።
የተበተነው የጥሪ ወረቀት የሚከተለው ነው፤ ዘ-ሐበሻ የዚህን ስብሰባ ውጤት ተከታትላ ትዘግባለች።
zehabesha.com