Wednesday, February 20, 2013

Walga’ii Ji’aa WWDO


Walga’iin WWDO idleen Dilbata Gurraandhala 03, 2013, sa’aa 6:00w.b. irraa eegalee gaggeeffama. Akkuma barame sirna walga’ii keenya irratti qophiileen adda-addaa kan haala yeroon wal-qabatan qopha’anii jiru.

Kanaaf, dargaggoonni Oromoo Washington DC, Maryland (MD) fi Verginia (VA) keessa jiraattan walga’ii keenya ji’aa kana irratti argamuun sochiiwwan hojii jabeessoo ta’an ka dargaggooti hamlee guddaadhaan geggeessaa jiran irratti akka qooda fudhattan waamicha keenya kabajaa isiniif dabarsina.

Bashannanaa gamtaa keenya hojiin haa muli’fnu!

Bakki: Jaarmiyaa Hawaasa Oromoo,
6212 3rd Street, NW,
Washington, DC 20011

Sa’aatii: 6:00w.b.

Dargaggoon Oromoo Irree Oromoyaati!

Koree gidduu WWDO (Waldaa Walgargaarsa Dargaggoota Oromoo) irraa.
http://www.youtube.com/watch?feature=player_embedded&v=vTZynu5YN1k

Monday, February 18, 2013

አዜብ መስፍን የአዲስ አበባ ከንቲባ?


Azeb  Mesfin, wife of Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi
(ዘ-ሐበሻ) የቀድሟ ቀዳማዊ እመቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከዚህ ቀደም በምርጫ ትወዳድርበት የነበረውን የትግራይ ክልል በመተው በአዲስ አበባ ከተማ ለምርጫ እንደምትቀርብ ከወደ አዲስ አበባ የመጡ ዜናዎች አመለከቱ። “የአቶ መለስ ዜናዊን ሌጋሲ እኔ አስፈጽመዋለሁ” በሚል በአቶ መለስ የቀብር መታሰቢያ ፕሮግራም ላይ በድፍረት የተናገረችው ወ/ሮ አዜብ በአሁኑ ወቅት የፌደራሉ ፓርላማ አባል ብትሆንም ኢሕአዴግን ወክላ በመጪው የቀበሌና የወረዳ ምርጫ ላይ ኢሕ አዴግን በመወከል በበቂርቆስ ክፍለከተማ እንደምትወዳደር የዘ-ሐበሻ የአዲስ አበባ ዘጋቢዎች አስታውቀዋል።
በተለይ “አፍቃሬ ኢሕአዴግ” በመባል የሚታወቀው የአቶ ልደቱ አያሌው ኤዲፓ በዚህ ምርጫ ላይ ሙሉ በሙሉ ሳይሆን በከፊል ብቻ እንደሚሳተፍ ባሳወቀበት በዘንድሮው ምርጫ ከወ/ሮ አዜብ ጋር ይወዳደራል ተብሎ የሚጠበቀው የኢዴፓው ወንድወሰን ተሾመ ነው። አቶ ወንደሰን ተሾመ ኢዴፓ ብቸኛው ያቀረበው እጩ ሲሆን ይህም እጩ ከወ/ሮ አዜብ በሚወዳደሩበት የምርጫ ጣቢያ እንዲወዳደር የተደረገው የፖለቲካ ትርፍ ኢሕአዴግ ለማግኘት አስቦ ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ትዝብታቸውን ለዘ-ሐበሻ ይገልጻሉ።
ባልተለመደ መልኩ ከትግራይ ክልል ተነስታ በአዲስ አበባ ከተማ ለምርጫ የምትወዳደረው ወ/ሮ አዜብ ምርጫው የተበላ እቁብ በመሆኑ በቀጥታ አሸንፋ የአዲስ አበባ ካቢኔ ውስጥ በመግባት የኦሕዴዱን ኩማ ደመቅሳ ቦታ በመቀበል የከተማዋ ከንቲባ እርሷን ለማድረግ የታቀደ ነገር እንዳለ ያስታውቃል ያሉት ታዛቢዎች በተለይም ከሰሞኑ ከወ/ሮ አዜብ ጋር ቅርርብ አላቸው የተባሉ አንዳንድ የአዲስ አበባ መጽሔቶች “የሴት ጠ/ሚ/ር ማየት ናፈቀን” የሚል ጽሁፍ ሁሉ መጻፉን ከወ/ሮ አዜብ ወደ አዲስ አበባ ከንቲባ መምጣት ጋር አያይዘውታል – ታዛቢዎቹ።
አቶ አርከበ እቁባይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ በነበሩበት ወቅት በአዲስ አበባ የታዩ ለውጦችን ቢያደርጉም የአዲስ አበባ ሕዝብ በምርጫ 97 ወቅት “አርከበ ለከተማዋ እድገት ብትጥርም፤ ኢሕአዴግን ወክለህ ብቻ ስለመጣህ አንመርጥህም” የሚል ምላሽ ከህዝቡ አግኝቶ ኢሕአዴግ በምርጫው በ0 በተሸነፈበት ወቅት ከወ/ሮ አዜብ ጋር እንደማይዋደዱ የሚነገርላቸው አቶ አርከበ በባልየው በአቶ መለስ ዜናዊ “በአዲስ አበባ ላይ ቀለም ከመቀባት በስተቀር ያመጣኸው ለውጥ የለም” በሚል በስብሰባ ላይ በግልጽ ተሰድበው ነበር።
በአሁኑ ወቅት ሕወሃት በክፍፍል ላይ እንዳለ እየተዘገበ መሆኑ ይታወቃል። የአቶ ስብሃት እና የወ/ሮ አዜብ ግሩፕ በየፊናው ተፋጧል። አሁን ወ/ሮ አዜብን በአዲስ አበባ ከንቲባነት አማሎ ድርጅቱን የማዳን ሥራ እየተሰራ ነው የሚሉ የፖለቲካ ተንታኞች አሉ።

በአቶ አባይ ፀሐዬ የሚመራ ስውር ኃይል ፓትርያርክ አቡነ ሳሙኤል እንዲመረጡ ጫና እያደረጉ ነው


Abune samuel 6
(የዘ-ሐበሻ ምንጮች ስለ 6ኛው ፓትርያርክ ምርጫ ዛሬ የደረሱባቸው መረጃዎች) ሥርዓቱ ያዘጋጃቸው ኃይሎች “ሆን ተብሎ በሕዝብ የተመረጡ ለማስመሰል” በቡድንም ሆነ በተናጠል 6ኛው ፓትርያርክ አቡነ ሳሙኤል እንዲሁኑ ጥቆማ ማድረጋቸው በፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴው ላይ ጫና እየፈጠረ መሆኑንና ይህን የሚያደርገው በአቶ አባይ ፀሐዬ የሚመራ ስውር ኃይል እንደሆነ የዘ-ሐበሻ የቤተክህነት ምንጮች አስታወቁ።
በተለይም ለ6ኛው ፓትርያርክነት ከታጩት 5 ሰዎች ውስጥ የ4ቱ በካድሬነት (ቡድን በማሰባሰብ ደረጃ) ከአቡነ ሳሙኤል ያነሰ እንዲሆን የተደረገው ሴራ በመንግስት የታቀደ መሆኑን ያጋለጡት እነዚሁ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ብዙ ጊዜ መንግስትን በመተቸት የሚታወቁት አቡነ ገብርኤል በእጩነት የገቡት ምርጫውን ሚዛናዊ ለማስመሰል እንደሆነ ገልጸዋል። ሌሎቹ 3 እጩ ጳጳሳት ደግሞ እንደ አቡነ ሳሙኤል ከወያኔ ጋር ለረዥም ጊዜ በመሥራት ያገኙት የደህነትና የስለላ ሥራ ልምድ የሌላቸው እንዲሆን ሆን ተብሎ መደረጉን እነዚሁ ምንጮች ገልጸው የፓትርያርክ ምርጫው “ዓይን ባለው እና በሌለው” መካከል ነው ብለዋል። ምንጮቹ ይህን ሲያብራሩም “አቡነ ሳሙኤል በደህነነት ሥራ በቆዩባቸው ጊዜያት ቡድን በማሰባሰብና በማደራጀት አሁን ከታጩት አባቶች የላቁ ናቸው፤ ስለዚህ ዓይን ያለው ሰው ፓትርያርክ ሆኖ ይመረጣል ቢባልና ለውድድር ሁለት ዓይን ያለው፣ ዓንድ አይን ያለውና አይን የሌለው ቢቀርቡ የቱ ያሸንፋል?” ይላሉ።
በተለይ መንግስት ሆን ብሎ ባደራጃቸው ቡድኖችና ግለሰቦች አማካኝነት በሕዝብ እንደተመረጡ በማስመሰል አቡነ ሳሙኤልን እጩ 6ኛው ፓትርያርክ እንዲሆኑ በገፍ በማስጠቆም ላይ ሲሆን ይህን ጫና ተከትሎና 6ኛው ፓትርያርክ ማን እንደሚሆን ቀድሞ መታወቁ የሲኖዶሱን አባላት ወትሮም ወደነበረባቸው የዘር መከፋፈል ውስጥ ከቷቸዋል ያሉት የዘ-ሐበሻ ምንጮች በተለይ፦
1ኛ. ፓትርያክ ከሸዋ ፓትርያርክ መመረጥ አለበት የሚሉ ጳጳሳት(ወ እጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተብሎ ፓትርያርኩ ስለሚጠራና የአቡነ ተክለሃይማኖት መንበር ላይ ስለሚቀመጥ ከሸዋ ነው መመረጥ ያለበት በሚሉ)
2ኛ. ከወሎ ፓትርያርክ ተመርጦ አያውቅምና ከወሎ ይመረጥ በሚሉ ሊቃነ ጳጳሳት፤
3ኛ. ፓትርያርክ ከትግራይ ነው መመረጥ ያለበት በሚሉ የአቡነ ሳሙኤል ደጋፊ ቡድኖች ሲኖዶሱ ውስጥ መከፋፈል እንዳለ አጋልጠዋል።
የሲኖዶሱ አባቶች ምንም እንኳ እንደዚህ ያለ መቧደን ቢይዙም የመንግስት ባለስልጣናት በሚገኙባቸው ስብሰባዎች በፍራቻ አቋማቸውን በግልጽ ሳያሳዩ መክረማቸውን ያስታወቁት ምንጮች ከሀሙስ በኋላ ብዙ ነገሮች ጠርተው ይሄዳሉ ሲሉ የደረሱባቸውን መረጃዎች አድርሰውናል።
ይህ በ እንዲህ እንዳለ በከፍተኛ ጫና ውስጥ እንዳለ የሚነገርለት የፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የካህናቱና ምእመናኑ የፓትርያርክ ጥቆማ የመስጠቱ የጊዜ ሰሌዳ በዛሬው ዕለት ከ10፡00 በኋላ መጠናቀቁንና ከነገ የካቲት 9 ቀን ጀምሮ እስከ የካቲት 14 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ዕጩዎችን የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም ለሚካሄደው ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ለማቅረብ አስመራጭ ኮሚቴው ውይይቱን እንደሚቀጥል ባወጣው መግለጫ ላይ አስታውቋል። ለአቡነ ሳሙኤል የተካሄደው የጠቋሚዎች ዘመቻ የኮሚቴውን አባላት በሙሉ ማስጨነቁ ተገልጿል።