Sunday, April 28, 2013

10 Oromo-Norwegians Stage Protest Against Neo-Neftegna TPLF in Oslo – 11 Arrested for Civil Disobedience

Gadaa.com
According to a Norwegian paper dagbladet.no and Google Translate service, Oromo-Norwegians protested against TPLF officials who were holding a meeting at the luxurious 4-Star Radisson Blu Scandinavia Hotel in Oslo, Norway, on April 28, 2013. The paper also said 11 were arrested for a short-period for civil disobedience, a form of nonviolent protest.

The Neo-Neftegna TPLF, which has been militarily occupying Oromiyaa since 1991, was forced to cancel its meeting. TPLF is using the overseas meetings to divert the attention from the ongoing land-grabs (farmland thefts), deforestation and gross human rights violations, including lack of press freedom, in Oromiyaa and elsewhere in the colonized South in the Ethiopian empire.
More coverage here:
- The Gulele Post
- Ayyaantuu.com
Gadaa.com

Wednesday, April 24, 2013

“ፍየል ወዲህ…”

ይኸነው አንተሁነኝ
ሚያዚያ 23 2013

“ከእንግዲህ የገበሬው ችግር የርሃብ ችግር ሳይሆን የሚያመርተውን የተትረፈረፈ ምርት በርካሽ እንዳይጥለውና በገንዘብ መልክ የሚኖረው ገቢ እንዳያንስበት ነው፡፡” ባለራዕዩ መለስ ዜናዊ በዘመነ አካለ ስጋው የወሸከተው ደርዝ የሳተ ቃል
የተለያዩ መንግስታት ሕዝባቸውን ለማስተዳደርና ቁሳዊ መንፈሳዊና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት፣ የሀገራቸውን ጸጥታና ደህንነት አስጠብቆ ለመምራት፣ እንዲሁም ከሌላው ዓለም ጋር ጥቅምን ያገናዘበ ግንኙነት ለመመስረት የሚያግዙ የተለያዩ ፖሊሲዎችን ያጸድቃሉ ይተገብራሉም። አፈጻጸሙንም በተመለከተ የተለያዩ መመዘኛዎችን በማውጣት ይከታተላሉ፤ ተጠቃሚውን ምሕበረሰብ መሰረት ያደረገ የእርምት እርምጃዎችንም መውሰድ ከአንድ መንግስት ነኝ ከሚል አካል የሚጠበቅ ሃቅ ነው። ይህ ሲሆን እንግዲህ የተዘጋጁትን ፖሊሲዎች፣ አተገባበራቸውንና ሊያመጡ የሚችሉትን ውጤት በተመለከተ የሚወጡ መንግስታዊ ቅድሚያ መግለጫዎችም ሆኑ ማብራሪያዎች ከዚያም ሲያልፍ እቅዶችና የተስፋ ቃሎች በሙሉ በባለሙያ የተቃኙና በመሰረታዊ የትንበያ ሳይንስ የተዳሰሱ ሊሆኑ መቻላቸው አያጠያይቅም እጅግ በጣም ቢያንስ ሃላፊነትና ተጠያቂነት ለሚሰማቸው መንግስታት።
እስከ አሁን ያልነውን ሀቅ ይዘን ወደ ሀገራችን ስንመጣና ከላይ የተጠቀሰውን የባለራዕዩን ንግግር ከዚህ ሀቅ ጋር ስናወዳድር በፓርላማ የጭብጨባ አጀብ ሞቅታ፣ በጉሽ ጠላ ብርታት አልያም በምርቃና መንፈስ የተነገረ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር አይኖረንም። ምክንያቱም ያለ እረፍት ለዘመናት ስትታረስ የኖረችና ለምነቷን ያጣች የበሬ ግንባር የምታክል መሬት ይዞ ዓመት ሙሉ የሚቆዝምን ገበሬ የትኛው የግብርና ፖሊሲ የተትረፈረፈ ምርት ባለቤት ሊያደርገው እንደሚችል ከባለራዕዩ በቀር የሚያውቅ የለምና። ባለፉት ጥቂት ዓመታትም የታየው ገበሬው የተትረፈረፈ ምርቱን የሚሸጥበት ገባያ ሲያጣና እንደተባለውም በርካሽ ሲሸጠው ሳይሆን ልሰው የማያውቁ ልሰው ወይም ቀምሰው የማያውቁ ቀምሰው የእህል ዋጋ ከመቸውም በላይ ሲወደድ ነው። “የግፍ ግፍ…” እንደሚባለው ይራበውም ይጥማው ያችኑ ቁራጭ መሬት ይዞ የሚያዘግመውን ገበሬ ሕወሃት መራሹ ገዥ በልማትና ኢንቨስትመንት ሰበብ እያፈናቀለ ለልመናና ለባሰ ግፍና በደል እየዳረገው መሆኑ ሲታይ የባለራዕዩ ንግግር በሞቅታ እንጅ ጥናትን መሰረት ያደረገ እንዳልነበረ ያሳያል። የሚታየው ያገጠጠ እውነት ያረጋገጠውም ገበሬው ትርፍ አምርቶ ሲደሰት ሳይሆን ከትናንሽ እስከ ትላልቅ ከተሞቻችንን ወረራ በሚመስል መልኩ በስደት ሲያጥለቀልቅ ነው። የቀረውም
ከቀጣሪነት ወደ ተቀጠቀሪነት ደረጃ ወርዶ በገንዛ መሬቱ ላይ ለአረብና ለሕንድ ገበሬዎች አሽከር በመሆን የስቃይ ሂዎት ሲገፋ እንጅ ትርፍ አምርቶ ሲሻሻል አልታየም። ታዲያ ይህ እንግዲህ ከሕወሃት እጅግ ብዙ ደርዝ የሳቱ ቃሎች አንዱ መሆኑ ሲታወስ ወያኔ እውን የማይሆን የተስፋ ዳቦ እያሳየ ይገዛል ቢባል ማጋነን አይሆንም።
ሕወሃት የስኳር ዋጋ መወደድን አስመልክቶ ባሰራጨው ደርዝ የሳተ መግለጫ ስኳር ቀምሰው የማያውቁ በመቅመሳቸው ለጊዜው አቅርቦቱ ከፍላጎቱ ሊጣጣምልን አልቻለም ብሎ፤ ነገር ግን በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ቀመር ችግሩ በቅርብ ጊዜ እንደሚስተካከል ነግሮን ነበር። ዛሬ ታዲያ ከስድስትና ሰባት ዓመታት በሗላ ለኒያ በሻጉራ ለታሙት መከረኛ ያገራችን ገበሬዎች ይቅርና ለከተሜው  ሳይቀር ስኳር ማየት እንደ መስቀል ወፍ ሲናፈቅ ስናይ የህወሃት ባለስልጣናት ንግግር በግምትና በአቦሰጥ እንደነበር ምስክር አያሻንም። አሉ የሚባሉት ስኳር ፋብሪካዎች የሚያመርቱትና በዚሁ ምስኪን ሕዝብ ሰበብ ከውጭ የሚገባው ስኳር ግን ለሕወሃት ባለስልጣናትና ጥቅም ተጋሪዎች ሃብት ማካበቻ ሽልማቶች ሆነዋል።
እንዲሁ ከዓመታት በፊት በቀን ሶስቴ ትበላላችሁ ትጠግባላችሁም ተብሎ በጎጠኛው መለስ ተነግሮን ተንቢቱ ስቶ ጭራሽ በጊዜው ከነበረን ሃቃችን በታች ተምዘግዝገን በመውረድ ላይ እንገኛለን። መናገር የማይሰለቸው ሕወሃት ግን አሁንም ሊመጡ ስለሚችሉ የፍስሃ ዘመናት ደርዝ የሳቱ ቃሎችን ከመግባት አልቦዘነም። እንዲያው ነገር እንዳላበዛ እንጅ ዘመኑ የፌዴራሊዝም ነው ስለዚህም ክልሎች ራሳቸውን ያስተዳድራሉ፤ የፖለቲካውን ምህዳር እናሰፋለን ለዓለምም እንከን የለሽ ምርጫ እናሳያለንስ ተብሎ አልነበር። ደርዝ ከሳቱ አይቀር እንዲህ ነው።
የሃብትና የስልጣን ክፍፍልን በተመለከተም “የኢትዮጵያ የተለያዩ ብሔረሰቦች ሕዝቦች ለሃብትና ለስልጣን እኩል መብት አላቸው” በሚል ደርዝ በሳተ ቃሉ ያናፋ የነበረው ሕወሃት የሀገራችንን አብዛኛውን የንግድ እንቅስቃሴ የራሱ ንግድ ኤምፓየር በሆነው “ኤፈርት” አማካኝነት ተቆጣጥሮ ሁሉም የብርና የሳንቲም ኖቶች ወደ “ኤፈርት” ይፈሳሉ እያለን ይገኛል። ይህንንም በተሳካና ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማስፈጸም ከኤፈርት የስራ እንቅስቃሴ ጋር ግንኙነት ያላቸውን መስሪያ ቤቶች በዘረኛ አገዛዙና በራሱ ቁርጠኛ ሰዎች ተቆጣጥሮ የሃብትና የስልጣን ክፍፍሉን አንድ አቅጣጫ ብቻ ይዞ እንዲሄድ እያደረገው ነው።
የተመኘውንና የተናገረውን የመናዊነትን ቀርቶ ኢትዮጵያዊ ሳይሆን የጎጥ አለቃ እንደሆነ የተሰናበተውን ባለራዕዩን ገዥ ጨምሮ ብዙዎቹ የሕወሃት ሰዎች ነባራዊውን ርሃብ በዘነጋ ምኞት፣ ዓለም ያወቀውን ስደታችንን ባላስታወሰ ተስፋ፣ አቅማችንን ባላገናዘበ ጀብደኝነትና የፖለቲካ ጥቅም ፍለጋ ባምስት ዓመት አባይን እናቆማለን እያሉ ደርዝ ያልጠበቀ ቃል ይመግቡናል። ይህን ቃላቸውን ለማስፈጸም በሚልም ድህነት ያደቀቀውን ምስኪን ሕዝባችንን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንን ሳይቀር በዚሁ የሳተ ቃል ያባብላሉ። በየደረሱበት ከተከራዩት የስብሰባ አዳራሽ ተዋርደው የመባረራቸው የዜና ዘገባ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች እየደረሰን ቢሆንም። የሆነው ሆኖ ግን በእርግጥ የአባይ ግድብ ወሬ እውነት ከሆነ ምነው ታዲያ ከሀገራችን አልፎ በአፍሪካ ተወዳዳሪ ባለሃብት እየሆነ ከመጣው ኤፈርት ኩባንያ ሀብት ትንሽ ዘገን አልተደረገም? ወይስ ኤፈርት በሌላው የኢትዮጵያ ክፍል ለምለም ሳር እየጋጠች ትግራይ ላይ  እንደምትታለብ ላም የትግራይ ጎጠኞች ብቻ ነው? ግድቡም ከተሰጠው የግንባታ እድሜ ግማሽ የሚሆነውን እየጨረሰ ነው ስራው ግን ባለህበት እርገጥ እንደሆነ ከቃላት በላይ ማረጋገጫዎች አሉ። ታዲያ ይህስ ቢሆን ደርዝ የሳተ ቃል ላለመሆኑ ከዚህ በላይ ማረጋገጫ ማሳየት ያስፈልግ ይሆን።
ከሕወሃት ደርዝ የሳቱ ቃሎች ይልቅ ሀገራችን ብዙ አንገብጋቢና ያገጠጡ ችግሮች አሏት። ሕዝባችን ነጻ አልወጣም በጎጠኝነት የአገዛዝ ቀንበር ስር ይማቅቃል። በየዓመቱ ባስር ሽዎች የሚቆጠሩ ዘለው ያልተገቡ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በሕወሃት የተምታታ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ምክንያት ተስፋ አጥተው በስደት ዓለም እየተንከራተቱ ይገኛሉ። በሕወሃት ውስጠ ተንኮል የተነሳም የሀገር ውስጥ ስደተኛው የትየለሌ ሆኗል። ወደድንም ጠላንም ዛሬ በዓለም ፊት ከውርደት በታች ተዋርደን የዓለም መሳቂያዎች ሆነናል። ሕወሃት ግን በኛ ኪሳራ የንግድ ኢምፓሩን በአፍሪካና በዓለም ደረጃ እያስፋፋ ቀጥሏል። ይህ የሀገራችን ቀውጢ ወቅት እኛን ካላስነሳን፤ ይህ የሕዝባችን ችግር እኛን ካላነቃን፤ ምን በጽናት ሊያቆመንና ሊያስተባብረን ይችላል? ይጠቅማል ባልነው መንገድና ወቅት ሁሉ የሕወሃትን ጎጠኛ አገዛዝ የሚያዳክም  የሀገራችንን ሰላምና ጸጥታ የሚያስጠብቅና የሕዝባችንን ጥንካሬና ስነ ልቦና የሚያጠናክሩ እርምጃዎችን እንውሰድ። የኢትዮጵያዊነታችን ክብርና ኩራቱ ሀገራችን ከሕዝባችን ጋር በሰላም ተጠብቃ አስከኖረች ድረስ ብቻ ነውና።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *
You may use these HTML tags and attributes: <a href="" title=""> <abbr title=""> <acronym title=""> <b> <blockquote cite=""> <cite> <code> <del datetime=""> <em> <i> <q cite=""> <strike> <strong>


Breakin news****Mengistu Hailemariam died of massive heart attck today

According to the news from zimbabwe national tv report, the former bloody dictator, mengistu hailemariam suffered massive heart attack yesterday and rushed tohospital in Harare. He was already lost his conciousness by the time he arrived. In an effort to revive him the doctors put him on life support for 24 hours and latter he was pronounced dead at the hospital . http://www.newzimbabwe.com/
Details are being expected as a lot of mourners are being fled to his residence andhospital
Mengistu Hailemariam has Died at the age of 75. Born on May 21, 1937 Mengistu was a father of Three children, Tilahun Mengistu, Tigist Mengistu and Andenet Mengistu. Lt. Col. Mengistu Haile Mariam (born 1937) became the head of state of Ethiopia and chairman of the ruling military government after a 1974 revolution deposed Emperor Haile Selassie. He was also the head of the central committee of Ethiopia’s Socialist Workers Party. Mengistu resigned as head of state in 1991 and fled into exile in Zimbabwe
for more info click here http://www.topix.com/forum/world/ethiopia/TH3KM4GAFTGNQHGVI

Tuesday, April 23, 2013

April 27, 2013 – Minneapolis, and May 25th in DC: The 4th Annual East African Medical Relief Foundation Fundraiser Luncheon to Help the Nejo Hospital Project

The following is an event announcement from the East African Medical Relief Foundation (EAMRF).
Gadaa.com

Please join us Saturday, April 27th 2013, at 1pm for the 4th Annual East African Medical Relief Foundation (EAMRF) Fundraiser Luncheon to help the Nejo Hospital Project.
(Please note there’s a similar fundraising event in Washington DC on May 25th 2013; details to be posted soon).
We appreciate all your past support, and we hope that we can count on you again this year. EAMRF works because of you!
Our Fundraiser will take place at:
Seward Tower East, 2910 east Franklin Ave south, Minneapolis, 55406
There will be a silent auction and a major raffle. Tickets will be sold for $10 per person at the door.
In a country where most individuals make about one dollar per day, your contribution will have multiplied impact towards sustaining/thriving healthy lives/community. The Nejo Hospital staff and community welcome your contribution with grateful hearts.
Your generous contribution is greatly appreciated. All donations are tax deductible as East African Medical Relief Foundation (EAMRF) is 501(c) 3 non-profit organization.
- EAMRF

Monday, April 22, 2013

Oromia: Alert Forest Fire in Ilu Ababora

Jawar Mohammed | April 22, 2013
Alert Forest Fire ! Reports have been pouring to my inbox and email overnight stating that the UNESCO registered Yayu Forest, located in Ilu Ababora, has been burning for the last two weeks. Once again the government has imposed media blackout, according to several journalists working for the government TV and radio stations who have been prevented from reporting on the issue. Those of you in the region please send us more information and lets spread the news as to increase pressure on the authorities to act quickly.

Abet ft. Haile Roots - Ethiopia's First Girl Band

http://www.diretube.com/yegna/abet-ft-haile-roots-ethiopias-first-girl-band-video_bc2cb810b.html

Norway: Police stopped Woyane meeting in Tasta Bydelshus

To All Oromo Community,
The Oromo Community Organization (OCO) of the Washington D.C Metro Area has planned to host a dinner party and workshop on Saturday April 20, 2013 at 6:00 PM at the Oromo House (OCO).
The Main purpose of the dinner party is to raise funds that will help cover the monthly mortgage payment of the Oromo House .The dinner party is also intended to encourage fellow Oromos come together and discuss issues of common concern while enjoying our delicious traditional cuisine and drinks.
In addition, guests from the D.C Government’s office of African Affairs( OAA) will be addressing the audience on “Mental Health” topic as part of a series of workshops (TEAM-Think, Eat, Act and Move) that OAA is currently undertaking in collaboration with various D.C based community and faith based organizations.
Entrance tickets are available with OCO Board, Executive, and House Committee members. Tickets will also be available at the gate. The prices for the tickets are: $50.00 for couples, and $30.00 for single.
We, therefore, kindly invite you, your family and friends to the above-mentioned dinner party and workshop.
With Best Regards,
Oromo Community Organization (OCO)
6212 3rd ST, NW Washington
Phone: 202-234-11511
Website: www.oneoromo.org Email: info@oneoromo.org

Pirojaktiin Bishaan dhugaatii Arsii Nageellee eebbifame

Finfinnee  Ebla  13  2005 (Oromiyaa) Pirojaktiin Bishaan dhugaatii godina Arsii lixaa  aanaa Arsii Nageelleetti baasii birrii miliyoona 380  caaluun ijaaramaa ture har'a eebbifame.
Piroojaktiin bishaan dhugaatiin kun kan eebbifame qondaaltoota Mootummaa Naannoo Oromiyaafi bakka bu'aa koomishiinii gamtaa Awurooppaatiini.Ooganaan biiroo Bishaan Albuudaafi Iinarjii Oromiyaa siran eebbaarratti haasawa dhageessiisaniin hawaasni piroojaktii Bishaan dhugaatii kun kunuunsuudhaan akka itti fayyadamuuf hubachisaniru.
Pirojaktichi rakkoo bishaan dhugaatii gandoolee gara garaa aanaa Arsii Nageellee keessatti ummata darraraa turetti furmaata waaraa kan argamsiisu akka ta'e sirna eebbaarratti himameera.
Pirojaktii  Bishaanii kanaan  ummata aanichaa kama dhibba tokko caalutu fayyadama jedhameera. (FBC)

Sunday, April 21, 2013

Radio Afuura Biyyaa: Kabajaa Guyyaa Gootota Oromoo – Oslo, Norway, fi Wellington, New Zealand

Kabaja Guyyaa Gootota Oromoo (GGO) isa bara 2013 magaalota Oslo fi Wellington keessatti ta’e. Obbo Dhugoomsaa Dhugaasaa seenaa jaallewwan isaanii goototaa Oromoo qabsoo irratti kufanii kan isaan dubbatan, gaaffii fi deebii Dr. Dagafaa Abdiisaa woliin ta’e akkasumas kabaja GGO isa Wellington ilaalchisee gaaffii fi deebii Obbo Lalisaa Kumarraa bakka bu’aa ABO New Zealand woliin goone caqasaa.
Bosonn Yaayyuu ibiddaan manca’aa jira. Motummaan dirmannaa tokko hingoone. dhimma kana ilaalchisee Obbo Geetaachoo woliin haasaa nuti goone oduu keessatti argattu.
Gadaa.com

    

Comments

http://www.oromoliberationfront.org/News/2013/OLF_Statement_on_the_passing_away_of_Jaarraa_Abbaa_Gadaa-Amharic.pdf
http://www.youtube.com/watch?v=XNyyT8q6ges&list=UU19xoofcGld3SL2-tmRIdMw&index=6

GadaaTube: Ayantu and Rastam on OromoTV (Minneapolis) « GadaaTube

GadaaTube: Ayantu and Rastam on OromoTV (Minneapolis) « GadaaTube

Saturday, April 20, 2013

http://gadaa.com/GadaaTube/7561/2013/04/17/radio-afuura-biyyaa-oduu-kabajaa-guyyaa-gootota-oromoo-oslo-norway-fi-wellington-new-zealand/

ሰበር ዜና፣ በአባይ ስም ዶላር ለመሰብሰብ በሲውዲን የወያኔ አምባሳደር ወደ ኖርዌይ ተጉዛ ውርደት ተከናንባ ተመልሳለች



አምባሳደሯ በሁለት ወያኔዎች ታጅባ ስለ ፓስፖርትና፣ ስለ አባይ ግድብ ቦንድ መናገር ከመጀመሯ የኖርዌይ ኢትዮጵያውያን “የለም የለም ኢትዮጵያ ውስጥ በግፍ ስለታሰሩ፣ በዘራቸው ምክንያት በሀገራቸው እየተፈናቀሉ ስላሉት ወገኖቻችን በቅድሚያ ጥያቄ አለን” በማለት አምባሳደሯን ሰንገው ይይዟታል።
ስብሰባው የወያኔዋ ተወካይ ባሰበችው መንገድ መሄድ አልቻለም። ተረበሸ።
ግርግሩ በርትቶ በመጨረሻም አምባሳደሯ እና አጃቢዎቿ በፖሊሶች ታጅበው በመጡበት እግራቸው ተመልሰዋል።
ተጨማሪ ዘገባ ይኖረናል…
ተመሳሳይ ዜና
Norway Ethiopians demonstration
Ethiopians in Norway have held a great and spectacular demonstration opposing the recentevictions of ethnic Amharas from different parts of Ethiopia and demanding freedom in 

ሰበር ዜና፣ በአባይ ስም ዶላር ለመሰብሰብ በሲውዲን የወያኔ አምባሳደር ወደ ኖርዌይ ተጉዛ ውርደት ተከናንባ ተመልሳለች



አምባሳደሯ በሁለት ወያኔዎች ታጅባ ስለ ፓስፖርትና፣ ስለ አባይ ግድብ ቦንድ መናገር ከመጀመሯ የኖርዌይ ኢትዮጵያውያን “የለም የለም ኢትዮጵያ ውስጥ በግፍ ስለታሰሩ፣ በዘራቸው ምክንያት በሀገራቸው እየተፈናቀሉ ስላሉት ወገኖቻችን በቅድሚያ ጥያቄ አለን” በማለት አምባሳደሯን ሰንገው ይይዟታል።
ስብሰባው የወያኔዋ ተወካይ ባሰበችው መንገድ መሄድ አልቻለም። ተረበሸ።
ግርግሩ በርትቶ በመጨረሻም አምባሳደሯ እና አጃቢዎቿ በፖሊሶች ታጅበው በመጡበት እግራቸው ተመልሰዋል።
ተጨማሪ ዘገባ ይኖረናል…
ተመሳሳይ ዜና
Norway Ethiopians demonstration
Ethiopians in Norway have held a great and spectacular demonstration opposing the recentevictions of ethnic Amharas from different parts of Ethiopia and demanding freedom in 

Wednesday, April 10, 2013

“የኢህአዴግ እብሪትና ትዕቢት አገርንና ህዝብን የሚያጠፋ ነው

አቶ ግርማ በቀለ 33ቱ ፓርቲዎች ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ

ፍኖተ ነጻነት መጋቢት 21 ቀን 2005 ዓ.ም.
የዛሬው እንግዳችን አቶ ግርማ በቀለ ይባላሉ ፡፡ አቶ ግርማ በቀለ በቅርቡ የትብብር ሠነድ የተፈራረሙት 33ቱ ፓርቲዎች ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ እና የኦሞ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ህብረት /ኦህዴህ/የተባለ ፓርቲ ሊቀመንበር ናቸው፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ፔቲሽን ፈራሚ ፓርቲዎች አሁን በምን እንቅስቃሴ ላይ ናቸው?
Ato Girma Bekele opposition politician based in Ethiopia
አቶ ግርማ በቀለ 33ቱ ፓርቲዎች ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ
አቶ ግርማ፡- የፔቲሽን ፊርማው ወደ ትብብር ሠነድ ከተሸጋገረ በኃላ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የቀጣይ 6 ወራት ተግባር እቅድ ተዘጋጅቷል፡፡ ትብብሩን ለሚቀጥለው 6 ወራት የሚመራ ቋሚ አስተባባሪ ኮሚቴ ለማስመረጥ በዝግጅት ላይ እንገኛለን፡፡ እስከ አሁን ድረስ ስንቀሳቀስ ሁሉም ነገር አልጋ በአልጋ አልነበረም፡፡ ከውስጥም ከውጪም የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመቋቋም እዚህ ደርሰናል፡፡ አሁን የደረስንበት ሁኔታ ተስፋ ሰጪ ነው፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ትብብሩ ስስ ነው፤ ትንሽ ቆይተው አለመግባብት ይፈጥራሉ፤ሁሉም አብረው አይዘልቁም የሚሉ ወገኖች አሉና እርስዎ ምን ይላሉ?
አቶ ግርማ፡- የማራቶን ውድድር አብረው የጀመሩ ሁሉ አይጨርሱም፡፡ እጅግ ውስብስብና ፈታኝ በሆነ ሠላማዊ ትግል አብሮ የጀመረ ሁሉ አብሮ ይጨርሰሳል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ ትግሉ እየጠራና እየገፋ በሄደ ቁጥር እየተራገፈና እየተንጠባጠበ ሊቀር ይችላል፡፡ እስከ አሁን በይፋ ለቅቄአለሁ ብሎ በይፋ መግለጫ የሰጠ ፓርቲ ባይኖርም በተግባር ግን እስአሁን አምስት ድርጅቶች ግንኙነታቸውን አቋርጠዋል፡፡ ነገ ሌላ ሊቀጥል ይችላል፡፡ 15 ወይም 20 ፓርቲ ነጥሮ ቢወጣ አያስገርምም ቁምነገሩ ቁጥሩ ላይ አይደለም ዋናው ቁም ነገር ፓርቲዎቹ ሕዝብና አገር የሚፈልገውን ተግባር እያከናወኑ ናቸው ወይ? የሚለው ነው፡፡ ከህዝብ የሚጠበቀው አመራሩን በቅርብ መከታተለና መቆጣጠር ነው፡፡ ድክመቶችንና ችግሮቹን ብቻ እየነቀሱ በማውጣት መተቸት ሳይሆን እኔንም ያገባኛል ብሎ ከትግሉ መቀላቀል ያስፈልጋል፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ህዝብ ዘንድ እንዴት እንደርሳለን? ህዝቡንስ እንዴት ወደ ትግሉ እናስገባለን ብላችሁ ታስባላችሁ?
አቶ ግርማ፡- ኢህአዴግ ተቃዋሚዎች ከህዝብ እንዳይገናኙ የማያደርገው ጥረት የለም፡፡ ህገመንግስቱን ጥሶ የመሰብሰብ፣ የመደራጀት ፣ሠላማዊ ሠልፍ ማድረግ እየከለከለ ነው፡፡ እኛ ግን መብታችንን ተጠቅመን ትግላችንን እንቀጥላለን፡፡ ዛሬ ሙሉ ለሙሉ በሚባልበት ሁኔታ የሚዲያ አፈና ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጂ ያሉትን ሚዲያዎች ሁሉ እንጠቀማለን፡፡ የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎችን ድህረ ገጾችን በመጠቀም ዓላማችንን እናስተዋውቃለን፡፡ የየፓርቲዎችን መዋቅር እንጠቀምበታን፡፡ የሲቪክስ ማህበራትን መዋቅርም እንዲሁም የመንግስት ሚዲያዎችን እንጠቀማለን ፡፡ በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ እንጠቀማለን፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- የወቅቱን የአገሪቱን ተጨባጭ የፖለቲካ ሁኔታ እንዴት ይገልጹታል?
አቶ ግርማ፡- እንደ 33ቱ ፓርቲዎች በጋራ ገምግመን የደረስንበት ድምዳሜ የለም፡፡
ጥያቄህን እንደ ግል የማምንበትን ልመልስልህ፡፡ አገራችን ከፍተኛ ችግር ውስጥ የወደቀችበት ጊዜው ነው፡፡ አገራችን ዛሬ በማንኪያ የተያዘች፤ ከሥሯ ድንጋይ የሚጠብቃት እንቁላል ሆናለች፡፡ አገራችን በዚያ ድንጋይ ላይ ወድቃ እንዳትከሰከስ ሁላችንም እጃችንን ዘርግተን እንቁላሏን ለማዳን መጠባበቅ አለብን፡፡ የኢህአዴግ እብሪትና ትዕቢት አገርንና ህዝብን የሚያጠፋ ነው፡፡ የሀገራችን ሁኔታ አሁን ካለበት ወደ ባሰ ደረጃ እየተጓዘ ነው፡፡ ህዝብን እያገለለ ሚዲያን እያፈነ የተለየ ሐሳብ ያለውን ሰው እያጠፋ መጓዝ ይፈልጋል፡፡ ይህ ጉዞ እጅግ አደገኛ ነው፡፡ ህዝቡ ተረድቶታል፡፡ እባካችሁ ተባበሩና ምሩን ሲል ቆይቷል፡፡ እኛም ተባብረናል፡፡ ከእንግዲህ በቁርጠኝነት አገር የማዳን ሥራ መሥራት ይጠበቅብናል፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- አንዳንድ ወገኖች መንግስት በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ እየገባ ነው፣ የተወሰነን ብሔር ለማጥቃት የተነጣጠረ ዘመቻ ጀምሯል ይላሉ፡፡ እርስዎ ምን ይላሉ?
አቶ ግርማ፡- ከጅምሩ የዚህን መንግስት አነሳስ ስንመለከት ገና በረሃ እያለ ዋና ጠላቶች ናቸው ብሎ የፈረጃቸው አሉ፡፡
ከብሔረሰብ አማራን ከሃይማት ኦርቶዶክስን በጠላትነት ፈርጇል፡፡ የብሔር ብሔረሰቦችን ጥያቄ ለመመለስ እነዚህን ሁለቱን ማጥፋት ያስፈልጋል ብሎ አቀደ፡፡ ሁለቱም የአገርና የህዝብ ጠላቶች ናቸው በማለት እንደዓላማ ወይንም እንደ አቅጣጫ አስቀመጠ፡፡ ከተለያየ ቦታ የተገኘ መረጃ የሚያለክተውም ይህንኑ ነው፡፡
ገና ትግራይ ውስጥ በነበሩበት ወቅት ከየቤተክርስቲያኑ ካህናትን በማባረር ቤተክርስቲያኖችን በካድሬ ቄሶች እንዲመሩና እንዲተዳደር አድርጓል፡፡ የመንግስት ሥልጣን ከያዙበት ቀን ጀምሮ በአማራውና በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ ሲፈፀም የነበረውን ሁሉ የምናውቀው ነው፡፡ ይህን መናገር ለቀባሪው ማርዳት ይሆናል፡፡
ሰሞኑን በአማራው ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውንም ይታወቃል፡፡ በቅርቡ ደግሞ የሃይማኖት ት/ቤታችንን ራሳችንን እናስተዳድር የሃይማኖት መሪዎቻችን እኛን አይወክሉም፤ መጅሊሳችንን ራሳችን እንሰይም፤ አህባሽ የተባለ ባዕድ አስተምሮ ከውጭ አምጥታችሁ አትጫኑብን፤ ብለው በሠላማዊ መንገድ የጠየቁ የተከበሩ የሙስሊሙ የሃይማት አባቶች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ድርጊት እየተመለከትን ነው፡፡ የሙስሊሙ ህብረተሰብ ለሠላማዊ ትግል አስተማሪ በሆነና በሠለጠነ መንገድ ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ ቆይተዋል፡፡
መማር ለሚችል ከሙስሊሙ ህብረተሰብ ትግስትና ሠላማዊ ተቃውሞን ተምሯል፡፡ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ህዝብን በሃይማኖት ከፋፍሎ ለማፋጀትና ዕድሜውን ለማራዘም ያደረገው ጥረት ከሽፎበታል፡፡
የሙስሊሙ ማህበረሰብ አባላት የጠየቁት ጥያቄ መንግስት በሃይማኖታቸው ጣልቃ እንዳይገባባቸው ነው፡፡ ስለዚህ መፍትሔው ከእንግዲህ ሙስሊሙ ክርስቲያኑ መላው የአገሪቱ ህዝብ እጅ ለእጅ ተያይዞ ይህን ሥርዓ ለመቀየር በቁርጠኝነት በጋራ መታገል ነው፡፡

የነፃነት ዋጋ በምን ይተመን?

እነሆ ዛሬ የምንጓዘው ከሳሪስ አቦ ወደ ቃሊቲ መናኽሪያ ነው። የሰው ልጅ ለኑሮ የሚደረግ ትርምስ ጎዳናው ላይ ይንቀለቀላል።
እንደወትሮው የኑሮ ንረት እያፍገመገመን ይኼው ዛሬ ላይ ደርሰናል። ‘ኑሮ ካሉት መቃብር ይሞቃል’ ያስብላል የአብዛኞቻችን አኗኗር ሲታይ። መኖርን መኖር ሊያስብሉ የሚችሉት መሠረታዊ ነገሮቻችን እስካሁን በጥያቄ ሰገነት ላይ እንደተሰቀሉ ናቸው። አንዳች ትንፋሽ እስኪያጠፋቸው እንደ ሻማ ውስጣችንን ያቀልጣሉ።

‹‹የዚህ ሁሉ ሰው ትዕግስት እንደ ሰም ቀልጦ ያለቀ ቀን ምን ልንሆን ነው?›› ይባባላል አንዳንዱ መንገደኛ እርስ በእርሱ እየተንሾካሾከ። ‹‹አይ እናት አገሬ! እስካሁን እኮ ለመኖር የተመኘ እንጂ የኖረ ትውልድ የለሽም። ይኼው እኛስ መቼ ከሰው ልጅ መሠረታዊ ፍላጎት (መጠለያ፣ ምግብ፣ ልብስ) ጥያቄ ተሻገርን?›› ይላል ታክሲ ጥበቃ አብሮኝ የቆመ ወጣት። ‘ወጣት ተስፋ ፍለጋ የባከነበት ዘመን’ ይላል ውስጤ የአዕምሮዬን የሐሳብ ልጓም ጥሶ። በዚያው ልክ ደግሞ ጥቂት የሚባሉት ኑሯቸውን ለሌሎች ኑሮ መቃናት ሰውተው ሲንገላቱ ጎዳናው ያሳየናል። አዎ፣ ግን ጥቂቶች ናቸው። እነርሱም አሸናፊ መሆን የሚችሉት የብዙኃንን ጥቅም ለግላቸው ተድላ ለማዋል የሚተጉ ተንኮለኞችን ሴራ መግታት ከቻሉ ብቻ ነው። ለመልካም ነገር የመተባበር ቅስም በተሰበረበት በዚህ ዘመን የበጎ ነገር አሸናፊዎችን ማየት ቀላል ነገር አልሆን ብሏልና። ‹‹የጎመን ድስት ይውጣ የገንፎ ድስት ይግባ›› ሲባል እንደሰማነው የግለሰቦች ዘመን ወጥቶ የሕዝብ ዘመን (በተግባር) ሲገባ የምናየው መቼ ይሆን? ‹‹ሊነጋ ሲል ይጨልማል›› ብለን ለጊዜው እንለፈው፡፡

በራሪ ታክሲ አግኝተን ተሳፍረናል። የቻለችንን ችላ የተረፉዋትን እንደበተነች ልትከንፍ በሾፌሯ አማካይነት ታክሲዋ ትጣደፋለች። በራሪ ነቻ! በበራሪ ዕድሜ በራሪ ታክሲ ማግኘት የሚቻለው ሲታደሉ ብቻ ነው። ሆኖም ወያላው እየጫነ የነበረው የአንዲት ተሳፋሪ ዕቃ ተጭኖ አላልቅ በማለቱ እየታገለ ቆመናል። ‹‹አቦ ምንድን ነው ይኼ? ከነገርኩሽ ብር ላይ ሦስት ብር መጨመርሽ ነው፤›› አላት ተማሮባት። ‹‹በእናትህ የለኝም። ሰው አገር ሲለቅ እንዲህ ነው የሚሸኘው?›› አለቸው የልምምጥ የውሸት ፈገግታ ገጿ ላይ ዘርግታ። ‹‹ታዲያ ይኼን ሁሉ ዕቃ በሰባት ብር? ደግሞ ሰው አጣብቤልሽ?›› አላት ሙግት በለመደ አንደበቱ። ‹‹ይኼን ጊዜማ እኛ ነን ሰበባችሁ? እኛን እንደ ዕቃ ቆጥራችሁ እንዳሻችሁ ወትፋችሁ ስትጭኑን ግን ምንም አይመስላችሁም?›› አለው አንድ ቁጡ ተሳፋሪ። ወያላው መልስ አልመለሰለትም። ወደ አንድ ጥቅስ ጠቆመውና ኮተቷ ወደአስቸገረው እንስት ዞሮ ‹‹እሺ በቃ ሁለተ ብር ትጨምሪያለሽ፤›› አላት። ‹‹አንተ በእናትህ? ምን ነው ምንም ቢሆን እኮ የኖርኩበት ከተማ ነው።

ዛሬ ብለቀው ጠብቀህ . . . ተው በእናትህ ገና ለትራንስፖርት ብዙ ነው የምከፍለው፤›› ትለዋለች። ጥቅስ የተጋበዘው ተሳፋሪ፣ ‹‹እኔን ነው በማያገባህ አትግባ? (ጥቅሱን እያነበበ) እንኳን አንተ መንግሥትም አላለኝ። የመናገር መብት አለኝ እሺ፤›› እያለ ይጦፋል፤ ቁጣ ቁጣ እያለው። ‹‹ወዴት ነው ስደቱ?›› ትላታለች ወፈር ያለችው ወጣት ተሳፋሪ በወያላው ካልከፈልሽ የምትባለዋን ምስኪን። ‹‹ወደ መተሃራ፤›› ትመልሳለች። ‹‹አገርሽ እዚያ ነው?›› ትጠይቃታለች። የወያላውና የንዴታሙ ንትርክ በመሀል ጎላ። ‹‹መንግሥት? አላለም እንዴ? ግለሰብ ከሕግ በላይ በሆነበት አገር፣ ጎሳ ከአገር ይበልጥ ይሰፋብናል በሚባልበት ጊዜ መንግሥት ይለኛል እንዴ!›› ወያላው ያመራል። ‹‹. . . አገሬስ እዚሁ ነበር። ምን ላድርግ ኑሮን አልቻልኩትም። ዘመዶቼ መተሃራ ናቸው። ኧረ ተይኝ እንግዲህስ ሁለተኛ ወደ እዚህ እግሬን የማነሳም አይመስለኝ፤›› ትላታለች ከሁላችንም ይልቅ ረጅም መንገድ ያቀደችዋ ምስኪን ተሳፋሪያችን። ለነገሩ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ሁሉም በመሰለው አቅጣጫ ለመሰደድ ያቆበቆ ነው። ግን ሽሽት ከምን? ከዘመን ወይስ ከአገር?

የወያላውና የደም ፍላታሙ ጎልማሳ አንድ ሁለት እየተካረረ ሄዶ ለቡጢ ከመጋበዛቸው በፊት እንዲረጋጉ አንድ ነገር ማድረግ ነበረብን። ወዲያውኑ ታክሲያችን መክነፍ ጀመረች። አንድ ቀልደኛ ‹‹አደራ ‘ኮብልስቶን’ አጠገባችሁ ካለ ገለል በማድረግ ተባበሯቸው፤›› ሲል ይቀልዳል። ‹‹አሁንማ ‘ከኤድስና ከኮብልስቶን ራሳችንን እንጠብቅ’ የሚል ‘ቢልቦርድ’ ሳያጥለቀልቀን ይቀራል?›› ይላል አጠገቡ የተቀመጠ የዚሁ ቀልደኛ ወጣት ብጤ። ‹‹ምን ነው ሰሞኑን ‘ኮብልስቶን’ ላይ ምን አዲስ ነገር ተገኝቶ ነው ቀልዱ?›› አለች ከኋላ መቀመጫ አራት ሆነን ከተቀመጥነው አንዷ። ‹‹አልሰማሽም (ጓደኛዋ ሳይሆን አይቀርም) ሰሞኑን በሥራ አለመግባባት በኮብልስቶን የተጨፋጨፉትን? አሁን መንግሥት ምን ይል ይሆን? ‘በአጎረስኩ እጄን ተነከስኩ’ ነው የሚለው መቼም፤›› አላት ለማሾፍ ድምፁን እያቀጠነና እያወፈረ።

‹‹ምን ይኼን ያህል ሞት ብርቅ ሆኖ ነው? እዳው የቤተሰብ ነው አይምሰልህ!›› አለችው። በዕድሜ ተለቅ ያሉ ተሳፋሪዎች በወያላውና በቁጡው ሰው መሀል ገብተው ነገሩን በማለዘብ ላይ ናቸው። ወፈር የምትለዋ እንስት ወያላው ሁኔታውን አይቶ ዕዳውን ያበዛባትን ምስኪን ሒሳብ ‹‹እኔ እከፍልሃለሁ፤›› ስትል እንሰማለን። አንዱ ሲገነባ አንደኛው ያፈርሳል። አንደኛው ሲሸሽ ሌላው ይሸኛል። የአንዱ መልካም ምላስ ቁጣን እያበረደ ይኖራል። የአንዱ ጦስ ለአንዱ የመኖር ትርጉም መሠረትነቱ እነሆ እንዲህ ይቀጥላል።

ወያላው በዕቃ በተጨናነቀው ሒሳብ መቀበያ መድረኩ ላይ እንደቆመ የመንገዱን ታሪፍ ሰብስቦ ጨርሷል። መሀል አካባቢ የተቀመጠ ተሳፋሪ ስልክ ጠራ። አነሳው፣ ‹‹ሃሎ፣ አቤት? ሃሎ . . . ሃሎ? አይሰማም፤›› ተዘጋ። ‹‹ወይ ‘ኔትወርክ’ እንዲህ በእንቁልልጭ ይጫወትብን ጎበዝ?›› ይላል ብሽቅ ብሎ። ‹‹የኑሯችን ባህሪ ነው። መልመድ ነው ያለን አማራጭ፤›› ትላለች ቀጭኗ መሀላችን የተቀመጠችው። ጓደኛዋ ይስቃል። (ደስ ይበላት ብሎ ይመስላል፣ ይሉኝታ!) ተደውሎለት የነበረው ተሳፋሪ ራሱ መልሶ ደውሎ ማናገር ጀምሯል። ‹‹ሄሎ አቤት አቤት! የት ደርሳችኋል? ምን? እናንተ ሰዎች ዓላማችሁ የሰውን እንጀራ መዝጋት ነው ልበል? አንዲት ‘ዋየር’ ለመቀጠል ይኼን ያህል መለመን አለብኝ? ያውም በራሳችሁ ጥፋት?›› እያለ ቀጠለ። የመብራት ኃይል ጣጣ መሆኑ ነው። ‹‹የፈረደበት፣ ባለፈው እኔም ዘንድ መብራት እልም ሲል አንዲት ገመድ ተቃጥላ መጥቶ ቆጣሪ ለማስተካከል ያየሁት አበሳ?›› በማለት አንድ አዛውንት ሮሮ ጀመሩ። መብራትና መብራት ኃይል ወዲያውኑ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆነው እርፍ።

‹‹እኔን የገረመኝ ኑና ሥሩልኝ ብላቸው የተመደቡት ሠራተኞች አራት ብቻ ናቸው ብለው የሰጡኝ መልስ ነው። አዲስ አበባን ለሚያህል ከተማ አራት ሰው ብቻ? ጉድ እኮ ነው የምንሰማው?›› ሲል አንድ ብርቱ መሳይ ጎልማሳ፣ ‹‹አሁንማ በተለይ ዝናብ ሲጥል ከመብረቅ ይልቅ የትራንስፎርመር ፍንዳታ መፍራት ጀመርን እኮ፤›› አለ ለመኮመክ ወጣቱ። ‹‹ኧረ ተው በፈጠራችሁ። አሁን ደሃን ማማት ደግ ነው? ምናለ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽ ዕቅዱ መሳካት ላይ ብናተኩር?›› ይላል አዲስ ድምፅ። ‹‹አይዞን ‘አሁን ዓባይ ሲገደብ መብራት መጥፋት የለ፣ ትራንስፎርመር መፈንዳት የለ፣ ሙስና የለ፣ የቤት ችግርና የመልካም አስተዳደር እጦት የለ፤ በቃ ሁሉንም ድራሹን ነው የምናጠፋው’ ይል ነበር ኢቲቪ መሀላችን ቢኖር ኖሮ!›› ብሎ ለመሳለቅ ሞከረ ወያላው። በሚኮረፈው ስንስቅ በሚሳቀው ስናኮርፍ ዕድሜና ጊዜ እንደሁ ላፍታም አልቆሙ። መጨረሻችን ግን ምን ይሆን?

ይልቅ ወደ ታክሲያችን መጨረሻ እየተጠጋን ነው። ቃል የሰለቸውን ዝምታ እየገለጸው ጥቂት እንደተጓዝን ወራጅ ባዩ እየተበራከተ ሄደ። ሳናውቀው በጨዋታ የፈጠርነው ዝምድና ለስንብት ሲጣደፍ ይታያል። ቀድመውን የሚወርዱት ተሳፋሪዎች እጅ ነስተውን ይሰናበታሉ። ‹‹አቤት! እውነት እኮ ሁሌ እንዲህ ብንዋደድ እኛን የመሰለ ጠንካራ፣ እንደኛ ሥልጡን የሚሆን ሕዝብ አልነበረም፤›› ይላሉ አዛውንቱ ታክሲ ውስጥ በአጭር ጊዜ የገነባነው የአንድነት መንፈስ ደስ አሰኝቷቸው። አጠገባቸው የተቀመጠ ጎልማሳ፣ ‹‹መዋደድ ማን ይጠላል ብለው ነው አባት? እንደሚያውቁት ግን እየመራ የሚያስጀምረን ከሌለ ከባድ ሕዝቦች ነን፤›› አላቸው። አልገባቸውም። ‹‹እንዴት?›› አሉት በከፊል ወደእሱ በመዞር። ‹‹ፍቅርን ከአንደበት ባለፈ በተግባር የሚያስተምረን አካል እንፈልጋለና። አዩ ሁሌም ሕዝብ ያለ መሪ፣ መንጋ ሁሌም ያለ እረኛ ዋጋ ኖሮት አያውቅም። ሆኖ የሚያሳየውና አርዓያ የሚሆንለት አካል ይፈልጋል ሕዝብ። ያኔ በዕድገት፣ በሥልጣኔና በልማት የሚያቆመው ምንም ነገር አይኖርም፤›› ሲላቸው ራሳቸውን ነቅንቀው ‹‹ትልቅ ነገር ተናገርክ።

በተለኝ እኛ በአሁኑ ጊዜ ከፖለቲካ ዲስኩር ይልቅ ተግባራዊ ዕርምጃ ነው ማየት የምንናፍቀው። ለሕዝብ ቆሜያለሁ ከሚል መንግሥት ሕዝባዊ ሥራ ማየት ናፍቆናል። ሙስና፣ የመልካም አስተዳደር እጦትና ጥልፍልፍ የቢሮክራሲ አሠራር አቅለሽልሾናል። እንኳን እሬት ማርም ሲበዛ ይመርም አይደል? እናም የምንፈልገው በነፃነት ኖረን በነፃነት መሞት ነው፡፡ ከነፃነት በተቃራኒ ያለው ባርነት ነው፤›› ብለውት ‹‹እኔን እዚህ ጋ ጣለኝ›› ሲሉ ታክሲዋ ቆመች። የነፃነት ዋጋ በምን ይተመናል እያልኩ ሳሰላስል ወያላው ‹‹እዚህ ነው መጨረሻው!›› ሲል መውረድ ግድ ሆነብን። መልካም ጉዞ!

Sunday, April 7, 2013

ማፈናቀሉ እስከመቼ?

ስራት ወልደሚካኤል
ህወሓት/ኢህአዴግ በህይወቱ ከሚፈራውና ከሚጠላው ነገር አንዱ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ ማየትና መስማት ነው፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱ አባላት በባህሪያቸው በውሸት፣ በተንኮልና በዕውቀት አስተሳሰብ አድማስ ደካማ ስለሆኑ የዜጎችን አንድነትና ብሔራዊነት ስሜትን አጥብቀው ይጠላሉ፤ ይህንንም በማሰራጨት የማሃይሞችን ርካሽ ፖለቲካ አራምደውበታል፣እያራመዱም ይገኛሉ፡፡ የዚህ ዋነኛ ተባባሪ ደግሞ በህወሓት የሚነዱት ብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴን ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የሀገሪቱን አንድነትና ደህንነት አደጋ ላይ በመጣላቸው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዝምታ ሊያልፍ ስለማይገባ እስካሁን ለፈፀሙት ሁሉ አስፈላጊውን ሰነድ በእጃችን ማስገባት፣ ድርጊቱን የፈፀሙትንና ተባባሪዎቹን ስም ዝርዝር ከነ ሙሉ አድራሻቸው መያዝ፣ ጉዳት የደረሰባቸውና ሚደርስባቸው ዜጎችን መርዳትና መንከባከብ እንዲሁም ወንጀለኞችን በተለያዩ ማኀበራዊ ሚዲያዎች(Facebook, blog, twitter,….) ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በማጋለጥ ለህግ እንዲቀርቡና ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ የሁላችንም ኢትዮጵያዊያን የውዴታ ግዴታ መሆን ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ዛሬ በሰፊው የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ በህወሓት/ኢህአዴግ እየደረሰ ያለው ግፍ በተመሳሳይ መልኩ ነገ በሌሎችም ላይ ይደርሳል፤ ከዚህ በፊትም ደርሷልና፡፡
ስለዚህ በቅርቡ በደቡብ ክልል ቤንች ማጂ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ለረጅም ጊዜ ሀብት ንብረት አፍርተውና ተዋልደው የኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎችን የማፈናቀል ስራ የተሰራውን መረጃ በሚመለከት ፣
አሁን ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያሶ ወረዳ እንዲፈናቀሉ የተደረጉት የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ለሞት.ለስቃይና ለመከራ እንዲደረጉ የተደረገበትን ምክንያት በዝርዝር በማጣርት መረጃውን ይፋ በማድረግ ሁሉም ዜጋ በጋራ ሊያወግዝና የተፈናቀሉትም ወደነበሩበት ስፍራ በክብር እንዲመለሱ ለማድረግ በሀግር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ መስራት ይጠበቅብናል ብዬ አስባለሁ፡፡ ለዚህም በሀገር ውስጥ ያሉ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ ፖለቲከኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ወደስፍራው በመሄድ አስፈላጊውን ጥናት በማድረግ መረጃውን ለህዝብ ይፋ ማድረግና የድርጊቱ ፈፃሚዎችም በአስቸኳይ ለህግ እንዲቀርቡ አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ፣
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ይህን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ በማጋለጥ ለኢህአዴግ የሚደረገው የለጋሾች ድጋፍ ለሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሚውል ማረጋገጥና ድጋፉ እንዲቋረጥ ከማድረግ በተጨማሪ መረጃውን ለሚሰበስቡ ሀገር ውስጥ ላሉ ሀገር ወዳድ ሰባዓዊ ባለሙያዎች የገንዘብ፣ የቁሳቁስና የሙያ ድጋፍ ማድረግ፣
በተለይ ወንጀሉ የሚፈፀምባቸው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ወገኖቻችን ወኪል ነኝ የሚለውን ብአዴን/ኢህአዴግ አባላት ጉዳዩን አጥብቀው በመጠየቅ ለድርጅቱ የሚያደርጉትን ድጋፍ ሙሉ ለሙሉ በማቋረጥ ለህዝብ እና ለሀገር ያላቸውን ወገንተኝነት ማረጋገጥ፣ ከፓርቲውም በይፋ በመልቀቅ ህዝባዊ ዓላማ ያለውን ትግል መቀላቀልና የወንጀል ተባባሪ አለመሆናቸውን በተግባር በማሳየት ከነገ ተጠያቂነት እራሳቸውን ነፃ ማድረግ፣
የሌላው ማኀበረሰብ ኢትዮጵያዊያን ድርጊቱን በጋራ በማውገዝ አሁን እየተፈፀመ ያለው ዘግናኝና አሰቃቂ ወንጀል ወደ ሌሎችም መዛመቱ ስለማይቀር “ማፈናቀሉ እስከመቼ?” በሚል ሁሉም በጋራ በመንቀሳቀስ በራሱ ተስፋ የቆረጠውን ዘረኝነት አገዛዝ እርቃኑን በማስቀረት ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን በማፅናት የዜጎች ሰብዓዊ መብት በሙሉ መከበሩን ለማረጋገጥ የዜጎች ከሀገራቸው መፈናቀል፣ መሰደድ፣ በግፍ መታሰርና መገደል ማብቃት አለበት እላለሁ፡፡ አለበለዚያ ነገ ሁላችንም ከሀገራችን መፈናቀላችን አይቀሬ ስለሆነ ዛሬውኑ ቆም ብለን በማሰብ ማድረግ ያለብንን መወሰን ያለብን ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ማንም ኢትዮጵያዊነታችንን ሲፈልግ ወስዶ እንካችሁ፤ ሳይፈልግ ዜግነታችሁን እኔ የምሰጣችሁ ስፍር ብቻ ነው ሲሉ መፍቀድ ባርነትን ከመምረጥ ውጭ ምን ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን? እኔ በበኩሌ ባርነትን በፍፁም አልመርጥም፣ አልደግፍምም፡፡

ማፈናቀሉ እስከመቼ?

ስራት ወልደሚካኤል

ህወሓት/ኢህአዴግ በህይወቱ ከሚፈራውና ከሚጠላው ነገር አንዱ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ ማየትና መስማት ነው፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱ አባላት በባህሪያቸው በውሸት፣ በተንኮልና በዕውቀት አስተሳሰብ አድማስ ደካማ ስለሆኑ የዜጎችን አንድነትና ብሔራዊነት ስሜትን አጥብቀው ይጠላሉ፤ ይህንንም በማሰራጨት የማሃይሞችን ርካሽ ፖለቲካ አራምደውበታል፣እያራመዱም ይገኛሉ፡፡ የዚህ ዋነኛ ተባባሪ ደግሞ በህወሓት የሚነዱት ብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴን ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የሀገሪቱን አንድነትና ደህንነት አደጋ ላይ በመጣላቸው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዝምታ ሊያልፍ ስለማይገባ እስካሁን ለፈፀሙት ሁሉ አስፈላጊውን ሰነድ በእጃችን ማስገባት፣ ድርጊቱን የፈፀሙትንና ተባባሪዎቹን ስም ዝርዝር ከነ ሙሉ አድራሻቸው መያዝ፣ ጉዳት የደረሰባቸውና ሚደርስባቸው ዜጎችን መርዳትና መንከባከብ እንዲሁም ወንጀለኞችን በተለያዩ ማኀበራዊ ሚዲያዎች(Facebook, blog, twitter,….) ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በማጋለጥ ለህግ እንዲቀርቡና ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ የሁላችንም ኢትዮጵያዊያን የውዴታ ግዴታ መሆን ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ዛሬ በሰፊው የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ በህወሓት/ኢህአዴግ እየደረሰ ያለው ግፍ በተመሳሳይ መልኩ ነገ በሌሎችም ላይ ይደርሳል፤ ከዚህ በፊትም ደርሷልና፡፡
ስለዚህ በቅርቡ በደቡብ ክልል ቤንች ማጂ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ለረጅም ጊዜ ሀብት ንብረት አፍርተውና ተዋልደው የኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎችን የማፈናቀል ስራ የተሰራውን መረጃ በሚመለከት ፣
አሁን ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያሶ ወረዳ እንዲፈናቀሉ የተደረጉት የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ለሞት.ለስቃይና ለመከራ እንዲደረጉ የተደረገበትን ምክንያት በዝርዝር በማጣርት መረጃውን ይፋ በማድረግ ሁሉም ዜጋ በጋራ ሊያወግዝና የተፈናቀሉትም ወደነበሩበት ስፍራ በክብር እንዲመለሱ ለማድረግ በሀግር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ መስራት ይጠበቅብናል ብዬ አስባለሁ፡፡ ለዚህም በሀገር ውስጥ ያሉ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ ፖለቲከኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ወደስፍራው በመሄድ አስፈላጊውን ጥናት በማድረግ መረጃውን ለህዝብ ይፋ ማድረግና የድርጊቱ ፈፃሚዎችም በአስቸኳይ ለህግ እንዲቀርቡ አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ፣
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ይህን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ በማጋለጥ ለኢህአዴግ የሚደረገው የለጋሾች ድጋፍ ለሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሚውል ማረጋገጥና ድጋፉ እንዲቋረጥ ከማድረግ በተጨማሪ መረጃውን ለሚሰበስቡ ሀገር ውስጥ ላሉ ሀገር ወዳድ ሰባዓዊ ባለሙያዎች የገንዘብ፣ የቁሳቁስና የሙያ ድጋፍ ማድረግ፣
በተለይ ወንጀሉ የሚፈፀምባቸው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ወገኖቻችን ወኪል ነኝ የሚለውን ብአዴን/ኢህአዴግ አባላት ጉዳዩን አጥብቀው በመጠየቅ ለድርጅቱ የሚያደርጉትን ድጋፍ ሙሉ ለሙሉ በማቋረጥ ለህዝብ እና ለሀገር ያላቸውን ወገንተኝነት ማረጋገጥ፣ ከፓርቲውም በይፋ በመልቀቅ ህዝባዊ ዓላማ ያለውን ትግል መቀላቀልና የወንጀል ተባባሪ አለመሆናቸውን በተግባር በማሳየት ከነገ ተጠያቂነት እራሳቸውን ነፃ ማድረግ፣
የሌላው ማኀበረሰብ ኢትዮጵያዊያን ድርጊቱን በጋራ በማውገዝ አሁን እየተፈፀመ ያለው ዘግናኝና አሰቃቂ ወንጀል ወደ ሌሎችም መዛመቱ ስለማይቀር “ማፈናቀሉ እስከመቼ?” በሚል ሁሉም በጋራ በመንቀሳቀስ በራሱ ተስፋ የቆረጠውን ዘረኝነት አገዛዝ እርቃኑን በማስቀረት ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን በማፅናት የዜጎች ሰብዓዊ መብት በሙሉ መከበሩን ለማረጋገጥ የዜጎች ከሀገራቸው መፈናቀል፣ መሰደድ፣ በግፍ መታሰርና መገደል ማብቃት አለበት እላለሁ፡፡ አለበለዚያ ነገ ሁላችንም ከሀገራችን መፈናቀላችን አይቀሬ ስለሆነ ዛሬውኑ ቆም ብለን በማሰብ ማድረግ ያለብንን መወሰን ያለብን ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ማንም ኢትዮጵያዊነታችንን ሲፈልግ ወስዶ እንካችሁ፤ ሳይፈልግ ዜግነታችሁን እኔ የምሰጣችሁ ስፍር ብቻ ነው ሲሉ መፍቀድ ባርነትን ከመምረጥ ውጭ ምን ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን? እኔ በበኩሌ ባርነትን በፍፁም አልመርጥም፣ አልደግፍምም፡፡

ማፈናቀሉ እስከመቼ?

ስራት ወልደሚካኤልህወሓት/ኢህአዴግ በህይወቱ ከሚፈራውና ከሚጠላው ነገር አንዱ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ ማየትና መስማት ነው፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱ አባላት በባህሪያቸው በውሸት፣ በተንኮልና በዕውቀት አስተሳሰብ አድማስ ደካማ ስለሆኑ የዜጎችን አንድነትና ብሔራዊነት ስሜትን አጥብቀው ይጠላሉ፤ ይህንንም በማሰራጨት የማሃይሞችን ርካሽ ፖለቲካ አራምደውበታል፣እያራመዱም ይገኛሉ፡፡ የዚህ ዋነኛ ተባባሪ ደግሞ በህወሓት የሚነዱት ብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴን ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የሀገሪቱን አንድነትና ደህንነት አደጋ ላይ በመጣላቸው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዝምታ ሊያልፍ ስለማይገባ እስካሁን ለፈፀሙት ሁሉ አስፈላጊውን ሰነድ በእጃችን ማስገባት፣ ድርጊቱን የፈፀሙትንና ተባባሪዎቹን ስም ዝርዝር ከነ ሙሉ አድራሻቸው መያዝ፣ ጉዳት የደረሰባቸውና ሚደርስባቸው ዜጎችን መርዳትና መንከባከብ እንዲሁም ወንጀለኞችን በተለያዩ ማኀበራዊ ሚዲያዎች(Facebook, blog, twitter,….) ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በማጋለጥ ለህግ እንዲቀርቡና ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ የሁላችንም ኢትዮጵያዊያን የውዴታ ግዴታ መሆን ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ዛሬ በሰፊው የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ በህወሓት/ኢህአዴግ እየደረሰ ያለው ግፍ በተመሳሳይ መልኩ ነገ በሌሎችም ላይ ይደርሳል፤ ከዚህ በፊትም ደርሷልና፡፡
ስለዚህ በቅርቡ በደቡብ ክልል ቤንች ማጂ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ለረጅም ጊዜ ሀብት ንብረት አፍርተውና ተዋልደው የኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎችን የማፈናቀል ስራ የተሰራውን መረጃ በሚመለከት ፣
አሁን ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያሶ ወረዳ እንዲፈናቀሉ የተደረጉት የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ለሞት.ለስቃይና ለመከራ እንዲደረጉ የተደረገበትን ምክንያት በዝርዝር በማጣርት መረጃውን ይፋ በማድረግ ሁሉም ዜጋ በጋራ ሊያወግዝና የተፈናቀሉትም ወደነበሩበት ስፍራ በክብር እንዲመለሱ ለማድረግ በሀግር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ መስራት ይጠበቅብናል ብዬ አስባለሁ፡፡ ለዚህም በሀገር ውስጥ ያሉ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ ፖለቲከኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ወደስፍራው በመሄድ አስፈላጊውን ጥናት በማድረግ መረጃውን ለህዝብ ይፋ ማድረግና የድርጊቱ ፈፃሚዎችም በአስቸኳይ ለህግ እንዲቀርቡ አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ፣
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ይህን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ በማጋለጥ ለኢህአዴግ የሚደረገው የለጋሾች ድጋፍ ለሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሚውል ማረጋገጥና ድጋፉ እንዲቋረጥ ከማድረግ በተጨማሪ መረጃውን ለሚሰበስቡ ሀገር ውስጥ ላሉ ሀገር ወዳድ ሰባዓዊ ባለሙያዎች የገንዘብ፣ የቁሳቁስና የሙያ ድጋፍ ማድረግ፣
በተለይ ወንጀሉ የሚፈፀምባቸው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ወገኖቻችን ወኪል ነኝ የሚለውን ብአዴን/ኢህአዴግ አባላት ጉዳዩን አጥብቀው በመጠየቅ ለድርጅቱ የሚያደርጉትን ድጋፍ ሙሉ ለሙሉ በማቋረጥ ለህዝብ እና ለሀገር ያላቸውን ወገንተኝነት ማረጋገጥ፣ ከፓርቲውም በይፋ በመልቀቅ ህዝባዊ ዓላማ ያለውን ትግል መቀላቀልና የወንጀል ተባባሪ አለመሆናቸውን በተግባር በማሳየት ከነገ ተጠያቂነት እራሳቸውን ነፃ ማድረግ፣
የሌላው ማኀበረሰብ ኢትዮጵያዊያን ድርጊቱን በጋራ በማውገዝ አሁን እየተፈፀመ ያለው ዘግናኝና አሰቃቂ ወንጀል ወደ ሌሎችም መዛመቱ ስለማይቀር “ማፈናቀሉ እስከመቼ?” በሚል ሁሉም በጋራ በመንቀሳቀስ በራሱ ተስፋ የቆረጠውን ዘረኝነት አገዛዝ እርቃኑን በማስቀረት ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን በማፅናት የዜጎች ሰብዓዊ መብት በሙሉ መከበሩን ለማረጋገጥ የዜጎች ከሀገራቸው መፈናቀል፣ መሰደድ፣ በግፍ መታሰርና መገደል ማብቃት አለበት እላለሁ፡፡ አለበለዚያ ነገ ሁላችንም ከሀገራችን መፈናቀላችን አይቀሬ ስለሆነ ዛሬውኑ ቆም ብለን በማሰብ ማድረግ ያለብንን መወሰን ያለብን ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ማንም ኢትዮጵያዊነታችንን ሲፈልግ ወስዶ እንካችሁ፤ ሳይፈልግ ዜግነታችሁን እኔ የምሰጣችሁ ስፍር ብቻ ነው ሲሉ መፍቀድ ባርነትን ከመምረጥ ውጭ ምን ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን? እኔ በበኩሌ ባርነትን በፍፁም አልመርጥም፣ አልደግፍምም፡፡

የቆራሄ ጀግና አፈወርቅ ወልደ ሰማያት የፋሺስት ኢጣልያን ጦር የመከተ


ከዓለማየሁ አበበ ሽንቁጥ
(የቀድሞ አምባሳዳር)

ቤኒቶ ሙሶሉኒ ሀሙስ ማታ በ12 ሰዓት ላይ መስከረም 22 ቀን 1928 ዓ.ም. ከጽሕፈት ቤቱ ሰገነት ብቅ ብሎ በመቆም ንግግሩን ለመስማት ይጠባበቅ ለነበረው ለመላው የጣልያን ሕዝብ “ኢትዮጵያን ለ40 ዓመታት ታገስናት እንግዲህስ በቃ” ብሎ ረጅም የድንፋት ንግግር ሲያደርግ የሕዝቡ ደስታ እጅግ በጋለ መልኩ ይስተጋባ ነበር:: ይህም በተንቀሳቃሽ የፊልም ምስል በዓለም ዙሪያ ታይቷል፡፡ ለአገራቸው ተቆርቁዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን በቁጭትና በንዴት ይመለከቱታል፡፡ ይቀጥላል…

 http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/6871

Tuesday, April 2, 2013

ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ በቃሊቲዎች ክስ ቀረበባት!

አቤ ቶኪቻው
መምህርት እና ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ በቃሊቲ እስር ቤት የሚገኙትን የአስተዳደር እና የጥበቃ ሰራተኞች ትንቂያለሽ፣ትሰደቢያለሽ እንዲሁም “የምትሰሩትን በሚዲያ እና ድረ ገፆችReeyot Alemu, the 31 year-2012 Courage in Journalism Award winner. አጋልጣለሁ” ብለሽ ትዝቺያለሽ በሚል ክስ ቀርቦባት መጋቢት 25 /2005 ዓ.ም ቃሏን መስጠቷ ተሰማ፡፡
ጋዜጠኛይቱ ክሱን አስመልክቶ ቃሏን እንድተሰጥ የተጠየቀቸችው መጋቢት 19 /2005 ዓ.ም ምሽት ከመኝታዋ ተቀስቅሳ የነበረ ቢሆንም ከጠበቃዬ ጋር ሳልነጋገር ምንም የምሰጠው ቃል የለኝም በማለቷ እስከ መጋቢት 25 ሊዘገይላት ችሏል፡፡
ርዮት የተከሰሰችው በፌደራል ታራሚዎች አያያዝ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 139/1999 አንቀፅ 36 መ እና ሠ ላይ በተቀመጠው መሰረት ሲሆን ይህ አንቀፅ “ከባድ የዲሲፒሊን ቅጣት የሚያስከትሉ ድርጊቶች” ተብሎ የተዘረዘረ ነው፡፡
ርዮት ቅጣቱ ተግባራዊ ከተደረገባት፤
ከአንድ ወር እስከ አራት ወር ለሚደርስ ጊዜ በወዳጅ ዘመዶቿ እንዳትጎበኝ፤ ደብዳቤ እንዳትልክ እና እንዳትቀበል (ይሄ እንኳ አሁንም ተግባራዊ ተደርጎባታል) የእስር ቤቱን ቤተ መጻህፍት እንዳትጠቀም፣ በእስር ቤቱ በሚደረግ የጋራ ዝግጅት እና መዝናኛ ላይ እንዳትሳተፍ እንዲሁም ከአንድ ወር እስከ ሁለት ወር ለሚደርስ ጊዜ ለብቻ እስር ትዳረጋለች፡፡
እንዲህ ከሆነ ደግሞ ያቺ በቃሊቲዊቹ ውቃቢ ትፈቀድ የነበረች አመክሮም ልትከለከል ነው ማለት ነው፡፡
በነገራችን ላይ ወጣቱ ፖለቲከኛ ናትናኤልም በእስር ቤቱ እየደረሰበት ያለውን አበሳ በመቃወም የርሃብ አድማ ላይ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ አባላትም ቅጥ ያጣውን የእስር ስርዓት ሃይ ለማለት የርሃብ አድማ ላይ ናቸው፡፡
ወይ ጣጣ… ብዬ የራሴን አስተያየት በአዲስ መስመር አቀርባለሁ…
እኔ የምለው ግን ኢህአዴግ ምነው እንዲህ መካሪ አጣ…? እርሱ እኛን በስንቱ መከራ እንዳልመከረን እርሱን የሚመክረው ማጣቱ የሚገርም ነው፡፡
እስቲ አሁን በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎችን እስሩ አንሶ አሳር የሚያበላው ምን ይሁነኝ ብሎ ነው? እንደሰማነው በርካታ የህሊና እስረኞች በታመሙ ጊዜ የሚያክሟቸው የእስር ቤቱ ሀኪሞች “መግደል ነበር አንተን” “መጨረስ ነበር አንቺን” እያሉ ያስፈራራሉ፡፡ እውነቱን ለመናገር ይሄ የመጨረሻው ዘመን ምልክት ነውና ነቅታችሁ ጠብቁ፡፡ መንግስታችን “ባትሪ ሎው” እያለ ይመስለኛል!

- የሳውዲ መንግስት “ህገ ወጦችንና በህጋዊ ሸፋን ህግን ጣሱ” የሚባላቸውነን የውጭ ዜጎች ለማጥራት የተጀመረው ቀጣይ ዘመቻ

Asif Asim
ዜና ሳውዲ
- የሳውዲ መንግስት “ህገ ወጦችንና በህጋዊ ሸፋን ህግን ጣሱ” የሚባላቸውነን የውጭ ዜጎች ለማጥራት የተጀመረው ቀጣይ ዘመቻ ወደ ሁለት ሚሊዮን ነዋሪዎች ከሃገር እንደሚበረሩ በሳውዲ መገናኛ ብዙሃን በኩል ይገመታል. . . – ዘመቻው በዋና ከተማዋ በሪያድ ፣በጅዳ ፣ደማምና በተለያዩ ከተሞች ቀጥሏል- 130 ሸህ የሚደርሱ በሴት ሳውዲ ስም የተመዘገቡ ትናንሽና መካከለኛ ድርጅቶች በማጠራቱ ሂደት ይነካሉ . . .-ስጋት ያደረባቸው ርካታ ድርጅቶች እየተዘጉ ነው ፣ ያለአሰሪያቸው የሚሰሩትም ስራ እያቆሙ ነው. . .- የበርካታ ሀገር ቆንስላና ኢንባሲዎችዜጎቻቸውን ለጥንቃቄ በማማከር ላይ ሲሆኑ የአደጋ ጊዜ ግንኙነት የሚፈጥሩባቸውን መስመር ሳይቀር በማቅረብ ላይ ናቸው- ይህ ዘመቻ ኢትዮጵየውያን ህጋዊ ነዋሪዎችን ስጋት ላይ ጥሏል ! የኢናባሲና ቆንስል ምስሪያ ቤቶች ሊመክሩ ሊዘክሩም ሆነ መረጃ ሊያቀብሉ አልጠሩንም ! ሳይታሰብ ከቤተሰቡ ሊያፈናቅል የሚችል ዜጋ ስል በሰደት ሰላፈራው ሃብት ንብረትና ቤተሰብ ደህንነት ጠበቃ የመቆም ማነው? ለምንስ ቆንስልና ኢንባሲ አስፈለገን?

የሌንጮ ለታ አዲሱ ትግል – እንዴት?

ስለ ኦነግ ሲነሳ አብዛኞች በመገረም የሚናገሩትና ሚዛን የሚደፋው አስተያየት የሚሰነዘረው በድርጅቱ መከፋፈልና መበጣጠስ ሳይሆን ተለያይተውም አስመራን የሙጥኝ ያሉበት ምክንያት ነው። ኢህአዴግ ህጻን እያለ ሻዕቢያ እንዳሻው ይነዳው እንደነበር የሚያስታውሱ አስተያየት ሰጪዎች ከሽግግር መንግስት ምስረታ በኋላ ኦነግ አገር ለቆ እንዲወጣ መንገዱን የጠረገው ሻዕቢያ መሆኑንን በቁጭት ይናገራሉ።
ኢህአዴግ ለስልጣን አዲስ በሆነበት የጨቅላነት ዘመኑ፣ ኦነግ በታሪኩ ያልነበረውን ሰራዊት በመገንባት አስጨንቆት እንደነበር በመጠቆም በወቅቱ አስተያየት የሰጡ ኢህአዴግ በተለይም መለስ በሻዕቢያ በኩል ኦነግን ለመታረቅ አቅርበውት የነበረውን የሽምግልና ጥያቄ ኦነግ እንዳይቀበል ሰሚ ባያገኙም በአጽዕኖት ምክራቸውን ሰጥተው ነበር።
በኦነግ ታጣቂ ሃይሎችና በኢህአዴግ ሰራዊት መካከል እኩል ሊባል በሚችል ደረጃ የጡንቻ መፈታተን ነበር። ደርግ ሲበታተን ኦነግን የተቀላቀሉ የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰራዊት አካላት ወያኔን የማዳፋት አቅሙ ነበራቸው። በወቅቱ የንስር ያህል ጉልበትና ሃይል ቢኖራቸውም ራሳቸውን ጫጩት አድርገው ተመለከቱ። አዲስ አበባ ሲገቡ የነበራቸውን የህዝብ ድጋፍ አራግፈው ጣሉት። በስሜት እየተነዱ ከሚወዷቸው ሁሉ ተቀያየሙ። ህወሃት አጋጣሚውን ለቅስቀሳና ለስም ማቆሸሻ ሰራበት። በስተመጨረሻ ኦነግ ሃይሉንና አቅሙን ዘንግቶ በአመራር ችግርና በአቋም ሸውራራነት ሃይሉን በሙሉ ወደ ካምፕ በማስገባት የኢህአዴግን የእርቅ ጥያቄ ተቀበለ። ሰራዊቱን እየነዳ በፈቃደኛት አሳሰራቸው።
በሻዕቢያ አደራዳሪነት ሁርሶ፣ ደዴሳና መስኖ የገባው ሰራዊት “በደባ” ተከቦ ትጥቁን እንዲፈታ ተደረገ። አብጦ የነበረው የኦነግ ጡንቻ በቅጽበት ከሰመ፤ ሰለለ። ኦነግ ሲቆጣጠራቸው የነበሩትን ቦታዎች ለማስተዳደርና በኦህዴድ ለመተካት ኢህአዴግ እንደ እባብ ተሹለክልኮ ዓላማውን አሳካ። ሻዕቢያም በዚሁ ውለታው ኢትዮጵያንና ኢኮኖሚዋን ብሎም የኢትዮጵያን ስነልቦና እንዳሻው እንዲጋልብ ተፈቀደለት። ብዙ አሻጥር ተፈጠረ፤ ተፈጸመም። ደንዳና ቆዳ ያላት ኢትዮጵያና ህዝቧ ተቦጠቦጡ። ተዘረፉ። አንድ እግር የቡና ተክል የሌላት ኤርትራ ቡና ላኪ ከሚባሉት ቀዳሚ አገራት ዝርዝር ውስጥ ተሰለፈች። አፈርን።
“አገሬን ከወራሪ አጸዳሁ” በማለት ከበሮ እየመታ ጦርነት አልቋል ብለው እጅ የሰጡ የወገን ወታደሮችን የረሸነው ሻዕቢያ ኢትዮጵያንም ያስተዳድር ጀመር። ዛሬ የሚማልባቸውና “ውርሳቸውን ሳናዛባ እናስጠብቃለን” የሚባልላቸው አቶ መለስ እንደ ባዕድ መሪ የኢትዮጵያን ክብርና ጥቅም ለሻዕቢያ አሳልፈው ሰጡ። የሻዕቢያ ታጣቂዎችና ኢትዮጵያ አብልታ ያሳደገቻቸው ጎረቤቶቻችን ሳይቀሩ ናጠጡብን። በየደጃቸው መሳሪያ ወደላይ እየተኮሱ በደስታ ውለታ ባስቀመጠችላቸው አገር ላይ ተሳለቁ። ምስኪኖችን ቤት እያስለቀቁ ወረሱ። የሌላቸውን ሃብትና ንብረት ሰበሰቡ። በኤርትራ ምድር በግፍ ለተረሸኑ የኢትዮጵያ ልጆች ተከራካሪ ጠፋና የሞት ሞት ሞቱ። አገራችን የግፈኞች መፈንጫ እንድትሆን መለስ በበረገዱት በር የገባው ሻዕቢያ ከርሱ ሲጎድል፣ “ልክህን እወቅ” የሚሉ ሲነሱ፣ ስርዓት ያዝ ሲባል ደሙ ተንተከተከና የሃይደር ህጻናትን በጠራራ ጸሃይ በላቸው። ትግራይን ወረረ። ሲሰርቁ ኅብረት የነበራቸው ሲከፋፈሉ ተጣሉና አገር ውርደት ገባው።
ይህንኑ ተከትሎ አገር አልበቃ ብሏቸው የነበሩና ወያኔን ሲያገለግሉ የነበሩ ቅጥረኞች የሰበሰቡትን ሳይበሉ ወደ “ከባርነት ናፅነት” ብለው ድምጻቸውን ወደሰጡላት “እናት አገራቸው ኤርትራ” ተጋዙ። ንብረታቸውን በትነው አገር ለቀው ወጡ። ከነጻነት በኋላ “ታይላንድ ትሆናለች፣ ሲንጋፖር ትሆናለች፤ ሆንግኮንግ ትሆናለች” በተባለላት አገራቸው ለመኖር ተገደዱ። ዳቦ ተሰልፈው ለመግዛት ታደሉ። ኬክ በለመደው፣ ቁርጥ በቆርጠው፣ “ሹካ ባስለመደው” እጃቸው ይድሁበት ገቡ። ወታደር ሆኑ። የሰገዱለትና ቅጥረኛ ሆነው ያገለገሉት ህወሃት መልሶ በረሃ በተናቸው። የሚያሳዝነው ግን ኤርትራዊያን ከየመንደሩ ተለቅመው ወደ አገራቸው ሲሄዱ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች አውቶቡስ ከብበው ደረት እየመቱ ያለቅሱላቸው ነበር። ደብቀው ያስቀሩዋቸውም አሉ። ጨርቃቸውን ጥለው አውቶቡስ እንዳይነሳ በፍቅር አምላክ የተንፈራፈሩ ነበሩ። ሁኔታውን የሚያስታውሱ ድርጊቱን “የሞኝ” ተግባር አድርገው ሲወሰዱት ሌሎች ደግሞ “ክፉ ላደረገብህ ክፉ አትመልስ” የሚለው ግብረገብነት የገባቸው የፈጸሙት የጀግንነት ተግባር ነው በማለት የአዲስአበባ ነዋሪዎችን የመንፈስ ልዕልና ያደንቃሉ፡፡
ይህ ከመሆኑ በፊት ጀምሮ ኦነግ ሻዕቢያን ሲለማመነውና እግሩን ሲልሰው የኖረ ድርጅት ዛሬ ድረስ ተበጣጥሶም እዛው አስመራ አምልኮ ደጅ ይገኛል። ከአመት ዓመት ያለ ለውጥ እዛው ይንፏቀቃል። እንደሚሰማው ከሆነ ወታደሮቹ የሻዕቢያ አግልጋዮች ሆነዋል። አመራሮቹም ቢሆኑ አስመራን ለቀው የመውጣትና እንዳሻቸው የመንቀሳቀስ መብት የላቸውም። በዚህም ይሁን በሌላ መነሻ ኤርትራ በከተሙት የተለያዩ የኦነግ ሃይሎች ላይ ከያቅጣጫው ስሞታ መቅረብ ከጀመረ ሰንብቷል። ኤርትራን ለቀው መውጣት አለባቸው የሚለው የኦሮሞ ልጆች ድምጽም በርክቷል። ጥያቄው አያሌ ፖለቲካዊ ማብራሪያ የሚጠይቅና አማራጭ መፍትሄ የሚያሻው ቢሆንም ኤርትራ ውስጥ አሉ በሚባሉ ታጣቂ ተቃዋሚዎች ያልተማረሩና ያልተሰላቹ ቢኖሩ አፍቃሪ ሻዕቢያዎች ወይም ራሳቸው የሻዕቢያ ሰዎች ወይም በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሻዕቢያን ዓላማ የሚያስፈጽሙ ብቻ ናቸው።
እንግዲህ በዚህ መሃል ነው አስመራን ተሳልመው ከነበሩት የኦነግ አመራሮች መካከል አቶ ሌንጮ ለታ፣ አቶ ዲማ ነገዎና ሌሎች ሰሞኑን አዲስ ዜና ይዘው ብቅ ያሉት። አዲስ ፓርቲ በማቋቋም ድፍረት የተሞላው አቋም በማራመድ “አዲሲቷን ኢትዮጵያ በጋራ ለመመስረት ተነስተናል። የቀድሞው የትግል ስልት አያዋጣም” ያሉት። ሃሳቡ መልካም ቢሆንም እንዴት? የሚለው ጥያቄ የበርካቶች ነው። ምክንያቱም በግልጽ “የቀጣዩ ትግል ሜዳ አገር ቤት ነው፤ አገር ቤት ገብተን እንታገላለን” ተብሏልና!
“የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር” ODF የሚባል አዲስ ግንባር መቋቋሙ ከአሜሪካ የሚኖሶታ ጠቅላይግዛት ከተሰማበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች እየተወረወሩ ሲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ጥርት ያለ መልስ አልተሰጠም። ግንባሩ መመስረቱ ይፋ ከሆነ በኋላ መጋቢት 22፤2005ዓም (ማርች 31/2013) በዚያው ጠቅላይግዛት በሚኒያፖሊስ ከተማ በተካሄደ ስብሰባ አንዳንድ ጉዳዮች ይፋ ሆነዋል።
ከብሪታንያ፣ ስዊትዘርላንድ፣ ከካናዳ፣ ከአውስትራሊያ፣ ከጀርመንና ከተለያዩ አገራት የተሰባሰቡ ቁጥራቸው 400 የሚጠጋ ተሰብሳቢዎች ባካሄዱት ውይይት አስፈላጊ የተባሉ ጥያቄዎች ተሰንዝረዋል። ኢትዮጵያን “ኢምፔሪያሊዝም፣ ቅኝ ገዢና ጠላት” አድርገው በመሳል ጥያቄ የሰነዘሩትን ጨምሮ ስለ ቀጣዩ ትግል ትግበራና ሰለ ኦሮሞ ህዝብ ነጻነት መከበር በስፋት ለተነሱ ጥያቄዎች አቶ ሌንጮ ለታ አስገራሚ መልስ ሰንዝረዋል።
“ያለፈውን በመውቀስ የትም አንደርስም። አሁን ማየትና ማሰብ ያለብን ወደፊት ነው። ሌሎች ወገኖችን አግልለን ብንታገል የትም አንደርስም። ያለፈው የትግል መንገድ ስህተት ነበር” ብለዋል። ስለ ኦሮሞ ህዝብ ነጻነት መከበር ሲናገሩ “የሁሉም ኢትዮጵያዊ መብት ካልተከበረ የኦሮሞ መብት ብቻውን ሊከበር አይችልም” በማለት መመለሳቸውን ለማወቅ ተችሏል።
“ጊዜው ተለውጧል። ጊዜው አዲስ ነው። አዲስ ምዕራፍ ላይ ነን። አዲሱ ምዕራፍ ለኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ነው” በማለት የተናገሩት አቶ ሌንጮ፣ “አገር ቤት እንዴት ገብቶ መታገል ይቻላል?” በሚል ለተነሳው ጥያቄ የሰጡት መልስ አዲሱን ድርጅታቸውንና እርሳቸውን የሚፈትን እንደሆነ ያመላከተ ነው።
ቀጣዩ ትግል ኤርትራ ላይ እንደማይሆን በግልጽ የተናገሩት አቶ ሌንጮ፣ አገር ውስጥ በመግባት ለማደራጀት፣ ለመታገል፣ ለመንቀሳቀስ ይቻል ዘንድ “መንገድ እንፈልጋለን” ብለዋል። ኢህአዴግ በተደጋጋሚ እንደሚለው ለድርድር የሚቀመጡ ወገኖች መጀመሪያ ህገመንግስቱን መቀበልና ህግመንግስቱን አክብሮ ለመስራት መማል አለባቸው። ይህ ወደፊት የሚታይ ቢሆንም አገር ቤት ለመግባትና ለመታገል እነ አቶ ሌንጮ ቢስማሙ እንኳን ሌላ መሰረታዊ ችግር እንዳለ ከወዲሁ እየተጠቆመ ነው።
በኦሮሞነታቸው በሚያነሱት ጥያቄ እስር ቤት የታጎሩ የኦሮሞ ልጆች ቁጥራቸው ከፍተኛ ነው – በአስር ሺዎች እንደሚቆጠር ይገመታል። በየቦታው ባሉ እስር ቤቶች ዋናው የመግባቢያ ቋንቋ ኦሮሚኛ እስከመሆን የደረሰበት ሁኔታ ነው የሚታየው። ይህ እውነታ ባለበት አቶ ሌንጮ የሚመሩት አዲሱ ድርጅት እንዴት አድርጎ ይታገላል? ወይም ደግሞ አባላቶቹ እስርና እንግልት እንዳያጋጣማቸው ምን ዓይነት ማረጋገጫና መተማማኛ ማግኘት ይቻላል?
“መልሱ ግልጽ ነው” በሚል ይመስላል “የፈለገው ቢመጣ፣ አስፈላጊው ህግን የጠበቀ ትግል ይካሄዳል። አገሪቱ ላይ ያለውን ህዝብ አስሮ ይችል እንደሆነ የሚታይ ይሆናል” የሚል እንደምታ ያለው ምላሽ ነው እየተሰነዘረ ነው ያለው። በሌላ በኩል አገር ቤት ገብቶ መታገል ብቸኛ አማራጭ ተደርጎ ሲወሰድ አዲሱ ጉዳይ የቀድሞው ሌሎችን ሲያገልና “ልዕልናና ነጻነት ለኦሮሞ ብቻ” በሚል የፖለቲካ ሾፌር ሲደወር የነበረው የትግል ስልት መቀየሩ ነው። በዚህም የተነሳ ይመስላል “ከማናቸውም በኢትዮጵያ ለዴሞክራሲ መረጋገጥና ለህዝብ እኩልነት ከሚሰሩ ድርጅቶችና ፓርቲዎች ጋር አብረን እንሰራለን። የቀድሞው መንገድ አይዋጣም” የሚል ምላሽ የሰጡት።
በኢትዮጵያ ፖለቲካ “እኔን ተከተል፣ ስትቃወም ከኔ ቀመር አትዛነፍ” የሚለውን አመለካከት ጨምሮ በድፍን የአንድ እንቅስቃሴ እርግጠኛ መነሻ ሳይታወቅ አስቀድሞ “የማብከትና የማበስበስ” ስራ መስራት የተለመደ በመሆኑ ከሁሉም ወገን እርጋታ እንደሚጠበቅ፣ ረጋ ብሎ መመርመር እንደሚያስፈልግ ከወዲሁ እየተነገረ ነው።
ላለፉት 20 ዓመታት ኢህአዴግ በብሄር እየለየ በፈጠረው ገደል እየተወረወሩ የሚገቡ ፖለቲከኞች በሰሩት ጥፋት ህዝብ ለከፍተኛ የአእምሮ ጉዳት ተዳርጓል። ኢህአዴግ የ50 ዓመት የቤት ስራ እንደሰጠ አድርጎ የሚያስበውም እነዚሁ የፖለቲካ መሪዎች የህወሃትን የሳሳ ፖለቲካ መረዳት ባለመቻላቸውና ከዋናው ጠላታቸው ይልቅ እርስ በርስ ለመቧቀስ የፈጠኑ መሆናቸውን በቀላሉ ስለሚያሳዩት ነው።
ከ40 ዓመታት የስህተት ጉዞ በኋላ አገር ቤት በመግባት “ሁሉም ነጻ ካልወጡ ኦሮሞ ብቻውን ነጻ አይወጣም” በሚል የትግል መርህ መነሳት በራሱ አስደሳች እንደሆነ አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል በስልክ ባደረጉት አጭር ቃለምልልስ ተናግረዋል።
“ድንበርና ክልልን ሳይሆን የምንጋራው አብሮነትን ነው” ያሉት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር “በዲኤንኤ ምርመራ ጎሳ አይታወቅም። ተመሳሳይ ዲኤንኤ ያላቸው ጎሳዎችም የሉም። ሁሉም ነጻ ካልወጡ ማንም ነጻ እንደማይወጣ መስማት ታላቅ ብስራት ነው” በማለት ከዓመታት ትግልና ውትወታ በኋላ ድርጅታቸው ሲታገልለትናሲሟገትለት የቆየው ዓላማ የሌሎችም መርህ ሆኖ በማየታቸውና በመስማታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ከኢትዮጵያ ሕዝብ አብላጫውን ቁጥር የሚይዘው የኦሮሞ ህዝብ ለዚህ ዓይነቱ መርህ ለዘመናት የቆየው ሥርዓቱም ሆነ አኗኗሩ ቅርብ እንደሆነ አቶ ኦባንግ አመልክተዋል፡፡ ድርጅታቸው ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ “ከጎሣ ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ እንስጥ” በሚል የከበረ መመሪያ ላይ ሲሰራ መቆየቱን የገለጹት አቶ ኦባንግ ከዚህ መመሪያ በተጨማሪ “ሁላችንም ነጻ ካልወጣን ማንም ብቻውን ነጻ ሊሆን አይችልም” በሚለው የትግል መርህ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቁመዋል፡፡ ይህንን መፈክር አሁን ደግሞ ኦሮሞ ወገኖቻችን ሲያነሱ መስማት ለድርጅታቸው ታላቅ ድል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ስብሰባው ላይ ማንም ሳይጠራቸው በራሳቸው አነሳሽነት እንደሄዱ ያስታወቁት አቶ ኦባንግ “የኦሮሞ ተወላጆች ስብሰባ ሲቀመጡ የሚነጋገሩት ስለ ኢትዮጵያ ነው። ኢትዮጵያዊ ነኝና ውይይቱ ይመለከተኛል። ስለዚህ ተገኘሁ። በደስታ ተቀበሉኝ። በስብሰባው ውስጥ በሰማሁት አዲስ ሃሳብ ተደሰትኩ” ብለዋል።
ላለፉት 20 ዓመታት አንዱ ስለ ሌላው ሲያወራ መኖሩን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ ሜቶ አሁን አንድ ላይ በመሆን ለመመካከርና “ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ” ግንባታ በጋራ ለመታገል መወሰን ከልምድ የተገኘ የፖለቲካ ተሃድሶ መሆኑን አስታውቀዋል። አያይዘውም ድሮም ቢሆን ፖለቲከኞች እንጂ ህዝብ አእምሮ ውስጥ ያልነበረ አስተሳሰብ በማቀንቀን ለህወሃት ፖለቲካ ማዳበሪያ የማቅረብ ስራ ሲሰራ እንደነበር አመልክተዋል።
አቶ ሌንጮ ለታ እንጀምረዋለን ያሉት አዲሱ መንገድ ሁሉንም ህዝብና የፖለቲካ ድርጅቶች ማዕከል በማድረግ ለመስራት ወስኖ የተነሳ እንደሆነ ሲያስታውቁ ያሰመሩበት ጉዳይ ቢኖር “ያለፈውን አናስብም። አሁን አዲስ ምዕራፍ ላይ ነን። አዲሱ ምዕራፍ ሁሉም የኢትዮጵያ ልጆች ተያይዘው የሚፈጥሯትን አዲስ አገር ማየት ነው፡፡” እርሳቸው እንዳሉት 40 ዓመት ባክኗል። አሁንም መንቃት አግባብ ነው። ነገር ግን ድጋፉም ሆነ ተቃውሞው በተራ የድጋፍና ተቃውሞ ስሜት ሳይሆን ረጋ ብሎ በመመርመር እንደሆነ የሚመክሩ ጥቂቶች አይደሉም።
(ፎቶዎቹን የወሰድነው ከ Hegeree Media channel ቪዲዮ ላይ ነው)