Saturday, April 20, 2013

http://gadaa.com/GadaaTube/7561/2013/04/17/radio-afuura-biyyaa-oduu-kabajaa-guyyaa-gootota-oromoo-oslo-norway-fi-wellington-new-zealand/

ሰበር ዜና፣ በአባይ ስም ዶላር ለመሰብሰብ በሲውዲን የወያኔ አምባሳደር ወደ ኖርዌይ ተጉዛ ውርደት ተከናንባ ተመልሳለች



አምባሳደሯ በሁለት ወያኔዎች ታጅባ ስለ ፓስፖርትና፣ ስለ አባይ ግድብ ቦንድ መናገር ከመጀመሯ የኖርዌይ ኢትዮጵያውያን “የለም የለም ኢትዮጵያ ውስጥ በግፍ ስለታሰሩ፣ በዘራቸው ምክንያት በሀገራቸው እየተፈናቀሉ ስላሉት ወገኖቻችን በቅድሚያ ጥያቄ አለን” በማለት አምባሳደሯን ሰንገው ይይዟታል።
ስብሰባው የወያኔዋ ተወካይ ባሰበችው መንገድ መሄድ አልቻለም። ተረበሸ።
ግርግሩ በርትቶ በመጨረሻም አምባሳደሯ እና አጃቢዎቿ በፖሊሶች ታጅበው በመጡበት እግራቸው ተመልሰዋል።
ተጨማሪ ዘገባ ይኖረናል…
ተመሳሳይ ዜና
Norway Ethiopians demonstration
Ethiopians in Norway have held a great and spectacular demonstration opposing the recentevictions of ethnic Amharas from different parts of Ethiopia and demanding freedom in 

ሰበር ዜና፣ በአባይ ስም ዶላር ለመሰብሰብ በሲውዲን የወያኔ አምባሳደር ወደ ኖርዌይ ተጉዛ ውርደት ተከናንባ ተመልሳለች



አምባሳደሯ በሁለት ወያኔዎች ታጅባ ስለ ፓስፖርትና፣ ስለ አባይ ግድብ ቦንድ መናገር ከመጀመሯ የኖርዌይ ኢትዮጵያውያን “የለም የለም ኢትዮጵያ ውስጥ በግፍ ስለታሰሩ፣ በዘራቸው ምክንያት በሀገራቸው እየተፈናቀሉ ስላሉት ወገኖቻችን በቅድሚያ ጥያቄ አለን” በማለት አምባሳደሯን ሰንገው ይይዟታል።
ስብሰባው የወያኔዋ ተወካይ ባሰበችው መንገድ መሄድ አልቻለም። ተረበሸ።
ግርግሩ በርትቶ በመጨረሻም አምባሳደሯ እና አጃቢዎቿ በፖሊሶች ታጅበው በመጡበት እግራቸው ተመልሰዋል።
ተጨማሪ ዘገባ ይኖረናል…
ተመሳሳይ ዜና
Norway Ethiopians demonstration
Ethiopians in Norway have held a great and spectacular demonstration opposing the recentevictions of ethnic Amharas from different parts of Ethiopia and demanding freedom in 

Wednesday, April 10, 2013

“የኢህአዴግ እብሪትና ትዕቢት አገርንና ህዝብን የሚያጠፋ ነው

አቶ ግርማ በቀለ 33ቱ ፓርቲዎች ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ

ፍኖተ ነጻነት መጋቢት 21 ቀን 2005 ዓ.ም.
የዛሬው እንግዳችን አቶ ግርማ በቀለ ይባላሉ ፡፡ አቶ ግርማ በቀለ በቅርቡ የትብብር ሠነድ የተፈራረሙት 33ቱ ፓርቲዎች ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ እና የኦሞ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ህብረት /ኦህዴህ/የተባለ ፓርቲ ሊቀመንበር ናቸው፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ፔቲሽን ፈራሚ ፓርቲዎች አሁን በምን እንቅስቃሴ ላይ ናቸው?
Ato Girma Bekele opposition politician based in Ethiopia
አቶ ግርማ በቀለ 33ቱ ፓርቲዎች ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ
አቶ ግርማ፡- የፔቲሽን ፊርማው ወደ ትብብር ሠነድ ከተሸጋገረ በኃላ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የቀጣይ 6 ወራት ተግባር እቅድ ተዘጋጅቷል፡፡ ትብብሩን ለሚቀጥለው 6 ወራት የሚመራ ቋሚ አስተባባሪ ኮሚቴ ለማስመረጥ በዝግጅት ላይ እንገኛለን፡፡ እስከ አሁን ድረስ ስንቀሳቀስ ሁሉም ነገር አልጋ በአልጋ አልነበረም፡፡ ከውስጥም ከውጪም የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመቋቋም እዚህ ደርሰናል፡፡ አሁን የደረስንበት ሁኔታ ተስፋ ሰጪ ነው፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ትብብሩ ስስ ነው፤ ትንሽ ቆይተው አለመግባብት ይፈጥራሉ፤ሁሉም አብረው አይዘልቁም የሚሉ ወገኖች አሉና እርስዎ ምን ይላሉ?
አቶ ግርማ፡- የማራቶን ውድድር አብረው የጀመሩ ሁሉ አይጨርሱም፡፡ እጅግ ውስብስብና ፈታኝ በሆነ ሠላማዊ ትግል አብሮ የጀመረ ሁሉ አብሮ ይጨርሰሳል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ ትግሉ እየጠራና እየገፋ በሄደ ቁጥር እየተራገፈና እየተንጠባጠበ ሊቀር ይችላል፡፡ እስከ አሁን በይፋ ለቅቄአለሁ ብሎ በይፋ መግለጫ የሰጠ ፓርቲ ባይኖርም በተግባር ግን እስአሁን አምስት ድርጅቶች ግንኙነታቸውን አቋርጠዋል፡፡ ነገ ሌላ ሊቀጥል ይችላል፡፡ 15 ወይም 20 ፓርቲ ነጥሮ ቢወጣ አያስገርምም ቁምነገሩ ቁጥሩ ላይ አይደለም ዋናው ቁም ነገር ፓርቲዎቹ ሕዝብና አገር የሚፈልገውን ተግባር እያከናወኑ ናቸው ወይ? የሚለው ነው፡፡ ከህዝብ የሚጠበቀው አመራሩን በቅርብ መከታተለና መቆጣጠር ነው፡፡ ድክመቶችንና ችግሮቹን ብቻ እየነቀሱ በማውጣት መተቸት ሳይሆን እኔንም ያገባኛል ብሎ ከትግሉ መቀላቀል ያስፈልጋል፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ህዝብ ዘንድ እንዴት እንደርሳለን? ህዝቡንስ እንዴት ወደ ትግሉ እናስገባለን ብላችሁ ታስባላችሁ?
አቶ ግርማ፡- ኢህአዴግ ተቃዋሚዎች ከህዝብ እንዳይገናኙ የማያደርገው ጥረት የለም፡፡ ህገመንግስቱን ጥሶ የመሰብሰብ፣ የመደራጀት ፣ሠላማዊ ሠልፍ ማድረግ እየከለከለ ነው፡፡ እኛ ግን መብታችንን ተጠቅመን ትግላችንን እንቀጥላለን፡፡ ዛሬ ሙሉ ለሙሉ በሚባልበት ሁኔታ የሚዲያ አፈና ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጂ ያሉትን ሚዲያዎች ሁሉ እንጠቀማለን፡፡ የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎችን ድህረ ገጾችን በመጠቀም ዓላማችንን እናስተዋውቃለን፡፡ የየፓርቲዎችን መዋቅር እንጠቀምበታን፡፡ የሲቪክስ ማህበራትን መዋቅርም እንዲሁም የመንግስት ሚዲያዎችን እንጠቀማለን ፡፡ በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ እንጠቀማለን፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- የወቅቱን የአገሪቱን ተጨባጭ የፖለቲካ ሁኔታ እንዴት ይገልጹታል?
አቶ ግርማ፡- እንደ 33ቱ ፓርቲዎች በጋራ ገምግመን የደረስንበት ድምዳሜ የለም፡፡
ጥያቄህን እንደ ግል የማምንበትን ልመልስልህ፡፡ አገራችን ከፍተኛ ችግር ውስጥ የወደቀችበት ጊዜው ነው፡፡ አገራችን ዛሬ በማንኪያ የተያዘች፤ ከሥሯ ድንጋይ የሚጠብቃት እንቁላል ሆናለች፡፡ አገራችን በዚያ ድንጋይ ላይ ወድቃ እንዳትከሰከስ ሁላችንም እጃችንን ዘርግተን እንቁላሏን ለማዳን መጠባበቅ አለብን፡፡ የኢህአዴግ እብሪትና ትዕቢት አገርንና ህዝብን የሚያጠፋ ነው፡፡ የሀገራችን ሁኔታ አሁን ካለበት ወደ ባሰ ደረጃ እየተጓዘ ነው፡፡ ህዝብን እያገለለ ሚዲያን እያፈነ የተለየ ሐሳብ ያለውን ሰው እያጠፋ መጓዝ ይፈልጋል፡፡ ይህ ጉዞ እጅግ አደገኛ ነው፡፡ ህዝቡ ተረድቶታል፡፡ እባካችሁ ተባበሩና ምሩን ሲል ቆይቷል፡፡ እኛም ተባብረናል፡፡ ከእንግዲህ በቁርጠኝነት አገር የማዳን ሥራ መሥራት ይጠበቅብናል፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- አንዳንድ ወገኖች መንግስት በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ እየገባ ነው፣ የተወሰነን ብሔር ለማጥቃት የተነጣጠረ ዘመቻ ጀምሯል ይላሉ፡፡ እርስዎ ምን ይላሉ?
አቶ ግርማ፡- ከጅምሩ የዚህን መንግስት አነሳስ ስንመለከት ገና በረሃ እያለ ዋና ጠላቶች ናቸው ብሎ የፈረጃቸው አሉ፡፡
ከብሔረሰብ አማራን ከሃይማት ኦርቶዶክስን በጠላትነት ፈርጇል፡፡ የብሔር ብሔረሰቦችን ጥያቄ ለመመለስ እነዚህን ሁለቱን ማጥፋት ያስፈልጋል ብሎ አቀደ፡፡ ሁለቱም የአገርና የህዝብ ጠላቶች ናቸው በማለት እንደዓላማ ወይንም እንደ አቅጣጫ አስቀመጠ፡፡ ከተለያየ ቦታ የተገኘ መረጃ የሚያለክተውም ይህንኑ ነው፡፡
ገና ትግራይ ውስጥ በነበሩበት ወቅት ከየቤተክርስቲያኑ ካህናትን በማባረር ቤተክርስቲያኖችን በካድሬ ቄሶች እንዲመሩና እንዲተዳደር አድርጓል፡፡ የመንግስት ሥልጣን ከያዙበት ቀን ጀምሮ በአማራውና በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ ሲፈፀም የነበረውን ሁሉ የምናውቀው ነው፡፡ ይህን መናገር ለቀባሪው ማርዳት ይሆናል፡፡
ሰሞኑን በአማራው ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውንም ይታወቃል፡፡ በቅርቡ ደግሞ የሃይማኖት ት/ቤታችንን ራሳችንን እናስተዳድር የሃይማኖት መሪዎቻችን እኛን አይወክሉም፤ መጅሊሳችንን ራሳችን እንሰይም፤ አህባሽ የተባለ ባዕድ አስተምሮ ከውጭ አምጥታችሁ አትጫኑብን፤ ብለው በሠላማዊ መንገድ የጠየቁ የተከበሩ የሙስሊሙ የሃይማት አባቶች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ድርጊት እየተመለከትን ነው፡፡ የሙስሊሙ ህብረተሰብ ለሠላማዊ ትግል አስተማሪ በሆነና በሠለጠነ መንገድ ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ ቆይተዋል፡፡
መማር ለሚችል ከሙስሊሙ ህብረተሰብ ትግስትና ሠላማዊ ተቃውሞን ተምሯል፡፡ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ህዝብን በሃይማኖት ከፋፍሎ ለማፋጀትና ዕድሜውን ለማራዘም ያደረገው ጥረት ከሽፎበታል፡፡
የሙስሊሙ ማህበረሰብ አባላት የጠየቁት ጥያቄ መንግስት በሃይማኖታቸው ጣልቃ እንዳይገባባቸው ነው፡፡ ስለዚህ መፍትሔው ከእንግዲህ ሙስሊሙ ክርስቲያኑ መላው የአገሪቱ ህዝብ እጅ ለእጅ ተያይዞ ይህን ሥርዓ ለመቀየር በቁርጠኝነት በጋራ መታገል ነው፡፡

የነፃነት ዋጋ በምን ይተመን?

እነሆ ዛሬ የምንጓዘው ከሳሪስ አቦ ወደ ቃሊቲ መናኽሪያ ነው። የሰው ልጅ ለኑሮ የሚደረግ ትርምስ ጎዳናው ላይ ይንቀለቀላል።
እንደወትሮው የኑሮ ንረት እያፍገመገመን ይኼው ዛሬ ላይ ደርሰናል። ‘ኑሮ ካሉት መቃብር ይሞቃል’ ያስብላል የአብዛኞቻችን አኗኗር ሲታይ። መኖርን መኖር ሊያስብሉ የሚችሉት መሠረታዊ ነገሮቻችን እስካሁን በጥያቄ ሰገነት ላይ እንደተሰቀሉ ናቸው። አንዳች ትንፋሽ እስኪያጠፋቸው እንደ ሻማ ውስጣችንን ያቀልጣሉ።

‹‹የዚህ ሁሉ ሰው ትዕግስት እንደ ሰም ቀልጦ ያለቀ ቀን ምን ልንሆን ነው?›› ይባባላል አንዳንዱ መንገደኛ እርስ በእርሱ እየተንሾካሾከ። ‹‹አይ እናት አገሬ! እስካሁን እኮ ለመኖር የተመኘ እንጂ የኖረ ትውልድ የለሽም። ይኼው እኛስ መቼ ከሰው ልጅ መሠረታዊ ፍላጎት (መጠለያ፣ ምግብ፣ ልብስ) ጥያቄ ተሻገርን?›› ይላል ታክሲ ጥበቃ አብሮኝ የቆመ ወጣት። ‘ወጣት ተስፋ ፍለጋ የባከነበት ዘመን’ ይላል ውስጤ የአዕምሮዬን የሐሳብ ልጓም ጥሶ። በዚያው ልክ ደግሞ ጥቂት የሚባሉት ኑሯቸውን ለሌሎች ኑሮ መቃናት ሰውተው ሲንገላቱ ጎዳናው ያሳየናል። አዎ፣ ግን ጥቂቶች ናቸው። እነርሱም አሸናፊ መሆን የሚችሉት የብዙኃንን ጥቅም ለግላቸው ተድላ ለማዋል የሚተጉ ተንኮለኞችን ሴራ መግታት ከቻሉ ብቻ ነው። ለመልካም ነገር የመተባበር ቅስም በተሰበረበት በዚህ ዘመን የበጎ ነገር አሸናፊዎችን ማየት ቀላል ነገር አልሆን ብሏልና። ‹‹የጎመን ድስት ይውጣ የገንፎ ድስት ይግባ›› ሲባል እንደሰማነው የግለሰቦች ዘመን ወጥቶ የሕዝብ ዘመን (በተግባር) ሲገባ የምናየው መቼ ይሆን? ‹‹ሊነጋ ሲል ይጨልማል›› ብለን ለጊዜው እንለፈው፡፡

በራሪ ታክሲ አግኝተን ተሳፍረናል። የቻለችንን ችላ የተረፉዋትን እንደበተነች ልትከንፍ በሾፌሯ አማካይነት ታክሲዋ ትጣደፋለች። በራሪ ነቻ! በበራሪ ዕድሜ በራሪ ታክሲ ማግኘት የሚቻለው ሲታደሉ ብቻ ነው። ሆኖም ወያላው እየጫነ የነበረው የአንዲት ተሳፋሪ ዕቃ ተጭኖ አላልቅ በማለቱ እየታገለ ቆመናል። ‹‹አቦ ምንድን ነው ይኼ? ከነገርኩሽ ብር ላይ ሦስት ብር መጨመርሽ ነው፤›› አላት ተማሮባት። ‹‹በእናትህ የለኝም። ሰው አገር ሲለቅ እንዲህ ነው የሚሸኘው?›› አለቸው የልምምጥ የውሸት ፈገግታ ገጿ ላይ ዘርግታ። ‹‹ታዲያ ይኼን ሁሉ ዕቃ በሰባት ብር? ደግሞ ሰው አጣብቤልሽ?›› አላት ሙግት በለመደ አንደበቱ። ‹‹ይኼን ጊዜማ እኛ ነን ሰበባችሁ? እኛን እንደ ዕቃ ቆጥራችሁ እንዳሻችሁ ወትፋችሁ ስትጭኑን ግን ምንም አይመስላችሁም?›› አለው አንድ ቁጡ ተሳፋሪ። ወያላው መልስ አልመለሰለትም። ወደ አንድ ጥቅስ ጠቆመውና ኮተቷ ወደአስቸገረው እንስት ዞሮ ‹‹እሺ በቃ ሁለተ ብር ትጨምሪያለሽ፤›› አላት። ‹‹አንተ በእናትህ? ምን ነው ምንም ቢሆን እኮ የኖርኩበት ከተማ ነው።

ዛሬ ብለቀው ጠብቀህ . . . ተው በእናትህ ገና ለትራንስፖርት ብዙ ነው የምከፍለው፤›› ትለዋለች። ጥቅስ የተጋበዘው ተሳፋሪ፣ ‹‹እኔን ነው በማያገባህ አትግባ? (ጥቅሱን እያነበበ) እንኳን አንተ መንግሥትም አላለኝ። የመናገር መብት አለኝ እሺ፤›› እያለ ይጦፋል፤ ቁጣ ቁጣ እያለው። ‹‹ወዴት ነው ስደቱ?›› ትላታለች ወፈር ያለችው ወጣት ተሳፋሪ በወያላው ካልከፈልሽ የምትባለዋን ምስኪን። ‹‹ወደ መተሃራ፤›› ትመልሳለች። ‹‹አገርሽ እዚያ ነው?›› ትጠይቃታለች። የወያላውና የንዴታሙ ንትርክ በመሀል ጎላ። ‹‹መንግሥት? አላለም እንዴ? ግለሰብ ከሕግ በላይ በሆነበት አገር፣ ጎሳ ከአገር ይበልጥ ይሰፋብናል በሚባልበት ጊዜ መንግሥት ይለኛል እንዴ!›› ወያላው ያመራል። ‹‹. . . አገሬስ እዚሁ ነበር። ምን ላድርግ ኑሮን አልቻልኩትም። ዘመዶቼ መተሃራ ናቸው። ኧረ ተይኝ እንግዲህስ ሁለተኛ ወደ እዚህ እግሬን የማነሳም አይመስለኝ፤›› ትላታለች ከሁላችንም ይልቅ ረጅም መንገድ ያቀደችዋ ምስኪን ተሳፋሪያችን። ለነገሩ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ሁሉም በመሰለው አቅጣጫ ለመሰደድ ያቆበቆ ነው። ግን ሽሽት ከምን? ከዘመን ወይስ ከአገር?

የወያላውና የደም ፍላታሙ ጎልማሳ አንድ ሁለት እየተካረረ ሄዶ ለቡጢ ከመጋበዛቸው በፊት እንዲረጋጉ አንድ ነገር ማድረግ ነበረብን። ወዲያውኑ ታክሲያችን መክነፍ ጀመረች። አንድ ቀልደኛ ‹‹አደራ ‘ኮብልስቶን’ አጠገባችሁ ካለ ገለል በማድረግ ተባበሯቸው፤›› ሲል ይቀልዳል። ‹‹አሁንማ ‘ከኤድስና ከኮብልስቶን ራሳችንን እንጠብቅ’ የሚል ‘ቢልቦርድ’ ሳያጥለቀልቀን ይቀራል?›› ይላል አጠገቡ የተቀመጠ የዚሁ ቀልደኛ ወጣት ብጤ። ‹‹ምን ነው ሰሞኑን ‘ኮብልስቶን’ ላይ ምን አዲስ ነገር ተገኝቶ ነው ቀልዱ?›› አለች ከኋላ መቀመጫ አራት ሆነን ከተቀመጥነው አንዷ። ‹‹አልሰማሽም (ጓደኛዋ ሳይሆን አይቀርም) ሰሞኑን በሥራ አለመግባባት በኮብልስቶን የተጨፋጨፉትን? አሁን መንግሥት ምን ይል ይሆን? ‘በአጎረስኩ እጄን ተነከስኩ’ ነው የሚለው መቼም፤›› አላት ለማሾፍ ድምፁን እያቀጠነና እያወፈረ።

‹‹ምን ይኼን ያህል ሞት ብርቅ ሆኖ ነው? እዳው የቤተሰብ ነው አይምሰልህ!›› አለችው። በዕድሜ ተለቅ ያሉ ተሳፋሪዎች በወያላውና በቁጡው ሰው መሀል ገብተው ነገሩን በማለዘብ ላይ ናቸው። ወፈር የምትለዋ እንስት ወያላው ሁኔታውን አይቶ ዕዳውን ያበዛባትን ምስኪን ሒሳብ ‹‹እኔ እከፍልሃለሁ፤›› ስትል እንሰማለን። አንዱ ሲገነባ አንደኛው ያፈርሳል። አንደኛው ሲሸሽ ሌላው ይሸኛል። የአንዱ መልካም ምላስ ቁጣን እያበረደ ይኖራል። የአንዱ ጦስ ለአንዱ የመኖር ትርጉም መሠረትነቱ እነሆ እንዲህ ይቀጥላል።

ወያላው በዕቃ በተጨናነቀው ሒሳብ መቀበያ መድረኩ ላይ እንደቆመ የመንገዱን ታሪፍ ሰብስቦ ጨርሷል። መሀል አካባቢ የተቀመጠ ተሳፋሪ ስልክ ጠራ። አነሳው፣ ‹‹ሃሎ፣ አቤት? ሃሎ . . . ሃሎ? አይሰማም፤›› ተዘጋ። ‹‹ወይ ‘ኔትወርክ’ እንዲህ በእንቁልልጭ ይጫወትብን ጎበዝ?›› ይላል ብሽቅ ብሎ። ‹‹የኑሯችን ባህሪ ነው። መልመድ ነው ያለን አማራጭ፤›› ትላለች ቀጭኗ መሀላችን የተቀመጠችው። ጓደኛዋ ይስቃል። (ደስ ይበላት ብሎ ይመስላል፣ ይሉኝታ!) ተደውሎለት የነበረው ተሳፋሪ ራሱ መልሶ ደውሎ ማናገር ጀምሯል። ‹‹ሄሎ አቤት አቤት! የት ደርሳችኋል? ምን? እናንተ ሰዎች ዓላማችሁ የሰውን እንጀራ መዝጋት ነው ልበል? አንዲት ‘ዋየር’ ለመቀጠል ይኼን ያህል መለመን አለብኝ? ያውም በራሳችሁ ጥፋት?›› እያለ ቀጠለ። የመብራት ኃይል ጣጣ መሆኑ ነው። ‹‹የፈረደበት፣ ባለፈው እኔም ዘንድ መብራት እልም ሲል አንዲት ገመድ ተቃጥላ መጥቶ ቆጣሪ ለማስተካከል ያየሁት አበሳ?›› በማለት አንድ አዛውንት ሮሮ ጀመሩ። መብራትና መብራት ኃይል ወዲያውኑ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆነው እርፍ።

‹‹እኔን የገረመኝ ኑና ሥሩልኝ ብላቸው የተመደቡት ሠራተኞች አራት ብቻ ናቸው ብለው የሰጡኝ መልስ ነው። አዲስ አበባን ለሚያህል ከተማ አራት ሰው ብቻ? ጉድ እኮ ነው የምንሰማው?›› ሲል አንድ ብርቱ መሳይ ጎልማሳ፣ ‹‹አሁንማ በተለይ ዝናብ ሲጥል ከመብረቅ ይልቅ የትራንስፎርመር ፍንዳታ መፍራት ጀመርን እኮ፤›› አለ ለመኮመክ ወጣቱ። ‹‹ኧረ ተው በፈጠራችሁ። አሁን ደሃን ማማት ደግ ነው? ምናለ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽ ዕቅዱ መሳካት ላይ ብናተኩር?›› ይላል አዲስ ድምፅ። ‹‹አይዞን ‘አሁን ዓባይ ሲገደብ መብራት መጥፋት የለ፣ ትራንስፎርመር መፈንዳት የለ፣ ሙስና የለ፣ የቤት ችግርና የመልካም አስተዳደር እጦት የለ፤ በቃ ሁሉንም ድራሹን ነው የምናጠፋው’ ይል ነበር ኢቲቪ መሀላችን ቢኖር ኖሮ!›› ብሎ ለመሳለቅ ሞከረ ወያላው። በሚኮረፈው ስንስቅ በሚሳቀው ስናኮርፍ ዕድሜና ጊዜ እንደሁ ላፍታም አልቆሙ። መጨረሻችን ግን ምን ይሆን?

ይልቅ ወደ ታክሲያችን መጨረሻ እየተጠጋን ነው። ቃል የሰለቸውን ዝምታ እየገለጸው ጥቂት እንደተጓዝን ወራጅ ባዩ እየተበራከተ ሄደ። ሳናውቀው በጨዋታ የፈጠርነው ዝምድና ለስንብት ሲጣደፍ ይታያል። ቀድመውን የሚወርዱት ተሳፋሪዎች እጅ ነስተውን ይሰናበታሉ። ‹‹አቤት! እውነት እኮ ሁሌ እንዲህ ብንዋደድ እኛን የመሰለ ጠንካራ፣ እንደኛ ሥልጡን የሚሆን ሕዝብ አልነበረም፤›› ይላሉ አዛውንቱ ታክሲ ውስጥ በአጭር ጊዜ የገነባነው የአንድነት መንፈስ ደስ አሰኝቷቸው። አጠገባቸው የተቀመጠ ጎልማሳ፣ ‹‹መዋደድ ማን ይጠላል ብለው ነው አባት? እንደሚያውቁት ግን እየመራ የሚያስጀምረን ከሌለ ከባድ ሕዝቦች ነን፤›› አላቸው። አልገባቸውም። ‹‹እንዴት?›› አሉት በከፊል ወደእሱ በመዞር። ‹‹ፍቅርን ከአንደበት ባለፈ በተግባር የሚያስተምረን አካል እንፈልጋለና። አዩ ሁሌም ሕዝብ ያለ መሪ፣ መንጋ ሁሌም ያለ እረኛ ዋጋ ኖሮት አያውቅም። ሆኖ የሚያሳየውና አርዓያ የሚሆንለት አካል ይፈልጋል ሕዝብ። ያኔ በዕድገት፣ በሥልጣኔና በልማት የሚያቆመው ምንም ነገር አይኖርም፤›› ሲላቸው ራሳቸውን ነቅንቀው ‹‹ትልቅ ነገር ተናገርክ።

በተለኝ እኛ በአሁኑ ጊዜ ከፖለቲካ ዲስኩር ይልቅ ተግባራዊ ዕርምጃ ነው ማየት የምንናፍቀው። ለሕዝብ ቆሜያለሁ ከሚል መንግሥት ሕዝባዊ ሥራ ማየት ናፍቆናል። ሙስና፣ የመልካም አስተዳደር እጦትና ጥልፍልፍ የቢሮክራሲ አሠራር አቅለሽልሾናል። እንኳን እሬት ማርም ሲበዛ ይመርም አይደል? እናም የምንፈልገው በነፃነት ኖረን በነፃነት መሞት ነው፡፡ ከነፃነት በተቃራኒ ያለው ባርነት ነው፤›› ብለውት ‹‹እኔን እዚህ ጋ ጣለኝ›› ሲሉ ታክሲዋ ቆመች። የነፃነት ዋጋ በምን ይተመናል እያልኩ ሳሰላስል ወያላው ‹‹እዚህ ነው መጨረሻው!›› ሲል መውረድ ግድ ሆነብን። መልካም ጉዞ!

Sunday, April 7, 2013

ማፈናቀሉ እስከመቼ?

ስራት ወልደሚካኤል
ህወሓት/ኢህአዴግ በህይወቱ ከሚፈራውና ከሚጠላው ነገር አንዱ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ ማየትና መስማት ነው፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱ አባላት በባህሪያቸው በውሸት፣ በተንኮልና በዕውቀት አስተሳሰብ አድማስ ደካማ ስለሆኑ የዜጎችን አንድነትና ብሔራዊነት ስሜትን አጥብቀው ይጠላሉ፤ ይህንንም በማሰራጨት የማሃይሞችን ርካሽ ፖለቲካ አራምደውበታል፣እያራመዱም ይገኛሉ፡፡ የዚህ ዋነኛ ተባባሪ ደግሞ በህወሓት የሚነዱት ብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴን ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የሀገሪቱን አንድነትና ደህንነት አደጋ ላይ በመጣላቸው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዝምታ ሊያልፍ ስለማይገባ እስካሁን ለፈፀሙት ሁሉ አስፈላጊውን ሰነድ በእጃችን ማስገባት፣ ድርጊቱን የፈፀሙትንና ተባባሪዎቹን ስም ዝርዝር ከነ ሙሉ አድራሻቸው መያዝ፣ ጉዳት የደረሰባቸውና ሚደርስባቸው ዜጎችን መርዳትና መንከባከብ እንዲሁም ወንጀለኞችን በተለያዩ ማኀበራዊ ሚዲያዎች(Facebook, blog, twitter,….) ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በማጋለጥ ለህግ እንዲቀርቡና ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ የሁላችንም ኢትዮጵያዊያን የውዴታ ግዴታ መሆን ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ዛሬ በሰፊው የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ በህወሓት/ኢህአዴግ እየደረሰ ያለው ግፍ በተመሳሳይ መልኩ ነገ በሌሎችም ላይ ይደርሳል፤ ከዚህ በፊትም ደርሷልና፡፡
ስለዚህ በቅርቡ በደቡብ ክልል ቤንች ማጂ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ለረጅም ጊዜ ሀብት ንብረት አፍርተውና ተዋልደው የኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎችን የማፈናቀል ስራ የተሰራውን መረጃ በሚመለከት ፣
አሁን ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያሶ ወረዳ እንዲፈናቀሉ የተደረጉት የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ለሞት.ለስቃይና ለመከራ እንዲደረጉ የተደረገበትን ምክንያት በዝርዝር በማጣርት መረጃውን ይፋ በማድረግ ሁሉም ዜጋ በጋራ ሊያወግዝና የተፈናቀሉትም ወደነበሩበት ስፍራ በክብር እንዲመለሱ ለማድረግ በሀግር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ መስራት ይጠበቅብናል ብዬ አስባለሁ፡፡ ለዚህም በሀገር ውስጥ ያሉ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ ፖለቲከኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ወደስፍራው በመሄድ አስፈላጊውን ጥናት በማድረግ መረጃውን ለህዝብ ይፋ ማድረግና የድርጊቱ ፈፃሚዎችም በአስቸኳይ ለህግ እንዲቀርቡ አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ፣
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ይህን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ በማጋለጥ ለኢህአዴግ የሚደረገው የለጋሾች ድጋፍ ለሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሚውል ማረጋገጥና ድጋፉ እንዲቋረጥ ከማድረግ በተጨማሪ መረጃውን ለሚሰበስቡ ሀገር ውስጥ ላሉ ሀገር ወዳድ ሰባዓዊ ባለሙያዎች የገንዘብ፣ የቁሳቁስና የሙያ ድጋፍ ማድረግ፣
በተለይ ወንጀሉ የሚፈፀምባቸው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ወገኖቻችን ወኪል ነኝ የሚለውን ብአዴን/ኢህአዴግ አባላት ጉዳዩን አጥብቀው በመጠየቅ ለድርጅቱ የሚያደርጉትን ድጋፍ ሙሉ ለሙሉ በማቋረጥ ለህዝብ እና ለሀገር ያላቸውን ወገንተኝነት ማረጋገጥ፣ ከፓርቲውም በይፋ በመልቀቅ ህዝባዊ ዓላማ ያለውን ትግል መቀላቀልና የወንጀል ተባባሪ አለመሆናቸውን በተግባር በማሳየት ከነገ ተጠያቂነት እራሳቸውን ነፃ ማድረግ፣
የሌላው ማኀበረሰብ ኢትዮጵያዊያን ድርጊቱን በጋራ በማውገዝ አሁን እየተፈፀመ ያለው ዘግናኝና አሰቃቂ ወንጀል ወደ ሌሎችም መዛመቱ ስለማይቀር “ማፈናቀሉ እስከመቼ?” በሚል ሁሉም በጋራ በመንቀሳቀስ በራሱ ተስፋ የቆረጠውን ዘረኝነት አገዛዝ እርቃኑን በማስቀረት ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን በማፅናት የዜጎች ሰብዓዊ መብት በሙሉ መከበሩን ለማረጋገጥ የዜጎች ከሀገራቸው መፈናቀል፣ መሰደድ፣ በግፍ መታሰርና መገደል ማብቃት አለበት እላለሁ፡፡ አለበለዚያ ነገ ሁላችንም ከሀገራችን መፈናቀላችን አይቀሬ ስለሆነ ዛሬውኑ ቆም ብለን በማሰብ ማድረግ ያለብንን መወሰን ያለብን ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ማንም ኢትዮጵያዊነታችንን ሲፈልግ ወስዶ እንካችሁ፤ ሳይፈልግ ዜግነታችሁን እኔ የምሰጣችሁ ስፍር ብቻ ነው ሲሉ መፍቀድ ባርነትን ከመምረጥ ውጭ ምን ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን? እኔ በበኩሌ ባርነትን በፍፁም አልመርጥም፣ አልደግፍምም፡፡