Saturday, March 19, 2016

በኦሮሚያ በየቦታው የአጋዚ ጦር አባላት እየተገደሉ እየተገኙ ነው – ግብር ሰብሳቢዎች “ህዝቡን ፈራን” አሉ


federal-police
 በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የአጋዚ ጦር አባላት እየተገደሉ እየተገኙ እንደሚገኙ ከተለያዩ ሥፍራዎች ለዘ-ሐበሻ የሚደርሱ መረጃዎች አመለከቱ:: ታክስ ሰብሳቢዎችም እንዲሁ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ቦታዎች ተዘዋውረው ግብር ለመሰብሰብ ሲሞክሩ በሚደርስባቸው ጥቃት የተነሳ ሥራ መስራት እንደተቸገሩም ለማወቅ ተቻለ::የዘ-ሐበሻ የመረጃ ምንጮች እንዳመለከቱት በ አርሲ በባሌ በምስራቅ እና ም ዕራብ ሐረርጌ, በምስራቅ ሸዋ; በ ም ዕራብ ሸዋ የተለያዩ ቦታዎች በየቀኑ የአጋዚ ጦር አባላት ባልታወቁ ሰዎች እየተገደሉ በየጫካው ሥር እንደሚገኙ ታውቋል””በም ዕራብ ሸዋ አምቦ; አመያና ግንደበረት ባለፉት 3 ሳምንታት ብቻ ከ6 በላይ የአጋዚ ጦር አባላት ተገድለው ተገኝተዋል:: እንደ አይን እማኞች ገለጻ በግንደበረት ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን አካባቢ የአጋዚ ጦር አባላት ላይ ህዝቡ እርምጃ እንደወሰደም ታውቋል::ከግንደበረት አካባቢ የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለከቱትም ህዝቡ ተፈትሮዋዊ ያልሆኑ ገደሎችን በመሥራት የአጋዚ ጦር መኪኖች ሲሄዱ እንዲገለበጡ በማድረግ ላይ እንዳለም ታውቋል:በአሪሲ ሮቤ; መርቲ; ገደብ; እና ኮፈሌም እንዲሁ የአጋዚ ጦር አባላት እየሞቱ እየተገኙ ሲሆን መንግስት ግን ይህን ደብቆ እንደሚገኝ ታውቋል::ይህ በ እንዲህ እንዳለ በኦሮሚያ የተለያዩ ቦታዎች ግብር ለመሰብሰብ የሚንቀሳቀሱ የመንግስት አካላት ላይ ሕዝቡ ጥቃት በማድረሱ የተነሳ ግብር ሰብሳቢዎች “ህዝቡን ፈራነው ስለዚህ ሄደን ግብር ክፈሉ ማለት አንችልም” በማለት ሥራ እንዳቆሙ ለመረዳት ተችሏል:: ግብር ክፍሉ እያሉ በም ዕራብ ሸዋና በምስራቅ ወለጋ የተንቀሳቀሱ የመንግስት አካላትን ሕዝቡ በቆመጥ ቀጥቅጦ እንዳባረረም ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች አመልክተዋል::ከም ዕራብ ወለጋ የደረሱን መረጃዎች እንደሚያመለከቱትም በተለይም በነጆ; በጃርሶና ጊምቢ አካባቢም ህዝቡ አድብቶ በመጠበቅ በአጋዚ ወታደሮች ላይ ጥቃቶችን እየፈጸመ ይገኛል::

No comments:

Post a Comment