Tuesday, April 2, 2013

- የሳውዲ መንግስት “ህገ ወጦችንና በህጋዊ ሸፋን ህግን ጣሱ” የሚባላቸውነን የውጭ ዜጎች ለማጥራት የተጀመረው ቀጣይ ዘመቻ

Asif Asim
ዜና ሳውዲ
- የሳውዲ መንግስት “ህገ ወጦችንና በህጋዊ ሸፋን ህግን ጣሱ” የሚባላቸውነን የውጭ ዜጎች ለማጥራት የተጀመረው ቀጣይ ዘመቻ ወደ ሁለት ሚሊዮን ነዋሪዎች ከሃገር እንደሚበረሩ በሳውዲ መገናኛ ብዙሃን በኩል ይገመታል. . . – ዘመቻው በዋና ከተማዋ በሪያድ ፣በጅዳ ፣ደማምና በተለያዩ ከተሞች ቀጥሏል- 130 ሸህ የሚደርሱ በሴት ሳውዲ ስም የተመዘገቡ ትናንሽና መካከለኛ ድርጅቶች በማጠራቱ ሂደት ይነካሉ . . .-ስጋት ያደረባቸው ርካታ ድርጅቶች እየተዘጉ ነው ፣ ያለአሰሪያቸው የሚሰሩትም ስራ እያቆሙ ነው. . .- የበርካታ ሀገር ቆንስላና ኢንባሲዎችዜጎቻቸውን ለጥንቃቄ በማማከር ላይ ሲሆኑ የአደጋ ጊዜ ግንኙነት የሚፈጥሩባቸውን መስመር ሳይቀር በማቅረብ ላይ ናቸው- ይህ ዘመቻ ኢትዮጵየውያን ህጋዊ ነዋሪዎችን ስጋት ላይ ጥሏል ! የኢናባሲና ቆንስል ምስሪያ ቤቶች ሊመክሩ ሊዘክሩም ሆነ መረጃ ሊያቀብሉ አልጠሩንም ! ሳይታሰብ ከቤተሰቡ ሊያፈናቅል የሚችል ዜጋ ስል በሰደት ሰላፈራው ሃብት ንብረትና ቤተሰብ ደህንነት ጠበቃ የመቆም ማነው? ለምንስ ቆንስልና ኢንባሲ አስፈለገን?

No comments:

Post a Comment