Friday, January 10, 2014

ዜና ድንቅ፦ ደቡብ አፍሪካዊው ሰባኪ ተከታዮቹ ሣር እንዲበሉ አዘዘ ....

ዜና ድንቅ፦ ደቡብ አፍሪካዊው ሰባኪ ተከታዮቹ ሣር እንዲበሉ አዘዘ .... (ሜይ ኦንላይን ጥር 2/2006- ጃንዋሪ 10/2014) (find the English version of this news on admas Ethiopia fb page)
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ የሚገኘው የራቢኒ ሴንተር ሚኒስትሪ ቤተክርስቲያን ፓስተር የሆኑት ሌሴጎ ዳንኤል፣ "ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ከፈለጋችሁ ውጡና የግቢውን ሳር ብሉ" ብለው በማዘዛቸው ተከታዮቻቸው ወጥተው ሳሩን ሲበሉ መዋላቸውን ሜል ኦንላይን ዘገበ። እንደዘገባው ከሆነ ፓስተሩ፣ ሥራ መብላት ወደ እግዚአብሔር ያቀርባል ከማለታቸው በተጨማሪ፣ ሰው ምንም ነገር ይሁን ወደ ሆድ የሚገባ እስከሆነ ድረስ መብላት ይችላልም ሲሉ ነግረዋቸዋል። ተከታዮቻቸውም ሳሩን ከበሉ በኋላ አብዛኞቹ ታመው ሲያስመልሳቸው ታይቷል።
ይህ ድርጊታቸው ግን በርካታ ተቃውሞ እንደቀሰቀሰባቸውም ዜናው አክሎ ገልጿል። (ከታችን በፎቶው ላይ ተክታዮቻቸው ሳሩን ሲበሉ ፣ .. ታመው ሲሯሯጡ እና ፓስተሩ ይታያሉ)
Lawn again Christians: South African preacher makes congregation eat GRASS to ‘be closer to God’
dailymail.co.uk
Under the instruction of Pastor Lesego Daniel of Rabboni Centre Ministries dozens of followers ate the grass at his ministry in Garankuwa, north of Pretect.

 
A South African preacher made his congregation eat grass to 'be closer to God' before stamping on them

No comments:

Post a Comment