Saturday, December 6, 2014

"ለኦሮሞ ወገኖቼ በተለይ ለወጣቱ ክፍል የተጻፈ ደብዳቤ"

በአፎሚአ ዮሴፍ
ቴድሮስ አፍሮ በ2005(97)< በ17 መርፌ> ብሎ የዘፈነው ዘፈን በምርጫው ወቅትና እና ከምርጫው ጋር ተያይዞ  በከተሞች እንዲሁም በአንዳንድ  የገጠር አከባቢዎች ሳይቀር ለተቀሰቀሱት ግጭቶችና በህወሀት ሀላፊዎች ትእዛዝ ሰጭነት ደማቸው በከንቱ ለፈሰሰው  ንጹሀን የድሀ ቤተሰቦች ልጆች እንደ ማቀጣጣያ ነዳጅነት ማገልገሉ የቅርብ ግዜ ትዝታ ነው። በወቅቱ በአብዛኛው ወጣት በተለይም በከተሞች አከባቢ በሚኖሩ ለውጥ ናፋቂዎች፣ነገር ግን ይመጣ ከነበረው ለውጥ ጋር ተያይዘው ስለሚመጡት ጉዳዮች ብዙም ንቃቱ ባልነበራቸውና ያላቸው ደግሞ ከፈለጉት ለውጥ ጋር ሊስተካከል የሚችል ጠንካራ የፓለቲካ ድርጅት ባለመኖሩ ምክንያት በዘፋኙ ባዶ ባዶ ግጥምች ታጅበው ወደ ሀገር የገቡትንና በወቅቱ
 የጠበቁት ሳይሆን ተቃራኒው ከወያኔ ሲገጥማቸው የሚኖሩበትን አፖርታማ ቆልፈው የተነጠቁትን ስልጣን በወሬ አሽንፈው ለመያዝ ካሉበት አሜሪካና አውሮፖ ተጠራርተው የመጡት ጎልማሶችና ሽማግሌዏች ወደ ጫካ ሳይሆን ወደመጡበት ተመልሰዋል ተከትሎዋቸው የፈሰሰውም ወጣት በዛ አሳዛኝ በሆነ ምልኩ ረግፎአል። ትኩረት ልሰጥ የፈለኩት ስላለፈው ምርጫ ወይም ከወራት በኋላ ስለሚደረገው የወያኔ የምርጫ ድራማ ሳይሆን በከተሞች አከባቢ ለሚኖረውና በአንድነት ስም ማንነቱን በብልጣብልጣብልጦች የውሽት የታሪክ ትምህርት እየተማረና እንደዳዊት እየደገመ ስላደገወና ግን ለምን ብሎ የመጠየቂያ ግዜ ላላግኘው የኦሮሞ ወጣት ነው። አሁን ግዜው self consciousness መጨመር ያለበትና ውሳኔዎችህ ከስሜታዊነት ርቀው በአጥጋቢ ምክንያት ላይ የተደገፉ መሆናቸውን የምታስተውልበት ነው።ምክንያቱም በገጠር ላለውና በወያኔ የሌቦችና የነጣቂ ቡድን መሬቱ እየተነጠቀበትና ከድህነት ወደ ባሰ ድህነት እየተሽጋገረ ላለው ምስኪን ድምጹ ሊሰማ ለማይችለው የኦሮሞ ገበሬድምጽ ልትሆንለት ምትችለው አንተ እና እኔ ድበምናደርገው መስዋእትነት ነው።ወደ እራስህ መመለስ አለብህ! ለምሳሌ ቀድሞ "በ17 መርፌ," "ጃ" ምናምን ብሎ የዘፈነውና አንተም ያለሱ ዘፋኝ የለም ብለህ የፈረምክለትና ምታፈቅረው ቴድሮስ አፍሮ ተብዬው የሌሎች መጠቀምያ አልያም ሆነ ብሎ አንተ በራስህ የታሪክ ተመራማሪ መሆን ሳያስፈልግህ እስካሁን ባሉት ስርአታት በደል ምክንያት እንደተዳፈነ እሳተ ገሞራ ዝም ያሉትን አያትህን ብትጠይቃቸው ሊነግሩህ ሚችሉትንና የነሱ "ጥቁር ንጕስ" (አቢሲኒያውያን) ላንተ ቅድመ አያቶች  ደግሞ ከአዎሮፓውያኑ በለመነው ነፍጥ "ጥቁር ሰይጣን" ሆኖ ኦሮሞ ወደሚኖርበት ምድር የመጣውንና እነሱ እንደሚዘፍኑለት ፍቅርን ሰበካ ሳይሆን አጠቃላይ የሆነ የማንነት ዘረፋና ይመሬት ቅርምትን ስትራቴጂ አድርጎ የተንቀሳቅሰውንና   እስካሁንም በኦሮሞ ምድርና በኦሮሞነት ላይ እየደረሰ ላለው ግፍና መከራ የመሰረት ድንጋይ ጥሎ ያለፈውን ንጉሳቸውን የመላእክት ገጸባህሪ አልብሶ  ባቀረበልህ ማግስትና በዛ ምክንያት በአብዛኛው የኦሮሞ ህዝብ ዘንድ የተቀሰቀሰበትn ቁጣ እንኳ ከቁብ ሳይቆጥር እንደገና በቅርቡ ባንድራው ላይ አንበሳው ከሌለ ምኑን ባንድራ ሆነ ብሎ ተመልሶ በዚህኛው የምርጫ ወቅት ብቅ ብሎዋል የአንበሳውም ልክት The lion of Juda(ሚገርመው አንበሳው ባለ ኮፍያ ነው ኮፍያውንም እሚሽለመው በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ብቻ መሆኑ ነው ሊሎቹ እምነቶች አይመለከታቸውም ማለት ነው)  የተፈሪ(ሀይለስላሴ) ስም ውስጥ እንዲህ ተብሎ ተካቷል The King of King The Elect Of God The Lion Of Juda ይህን ነው ዘፋኙና መሰሎቹ የሚፈልጕት ይህን ያደረገው በስህት አይደለም ኦንተ ደገሞ ኦሮሞ ነህ እነሱ የፈጠሩት የአፈታሪክ የስልጣን ተዋረድም ሀነ የዘር ግንድ ውስጥ የለህበትም you are just Oromo እኔ ልመራቹ ተፈጠርኩ የማትል ስለዚህ በዚህ ምርጫ ውስጥ እየተሳተፉ ካሉት ከመጋረጃው ጀርባ ሲታዩ ቁርጥ ቴዲ አፍሮንና ዘፍኖቹን ከሆኑ ድርጅቶች ላይ እራስህን አግልል ያንተ ተራ ሊመጣ ሚችለው አንተ ዛሬ ለራስህና ለተወለድክበት ማንነት በምታደርገው ትግል ነውና ትግልህን አካሄድና ከማን ጋር መጓዝ እንዳለብህ ጠንቅቀህ እወቅ  abstain yourself from making unnecessary sacrifices and undeserved love for the undeserved one!!!
ድል ለሰው ኦሮሞ ህዝብ!!!!
 

1 comment:

  1. በእርግጥ ያነሻቸው ሀሳቦች እውነትነት አላቸው!!!!!!!!!

    ReplyDelete